ያለፉት ሰማንያ ዓመታት ለእማማ ሁሉአገርሽ ተሰማ በጎና ምቹ አልነበሩም። በእነዚህ ጊዚያት አብዛኛው የህይወት መንገድ ጎርባጣና ሻካራማ ነበር። ወይዘሮዋ ያለፈውን በትዝታ መልሰው ሲያወጉት ከልብ ይከፋቸዋል፣ ያዝናሉ፣ ይተክዛሉ። እንደዋዛ ሰማንያ ዓመታት ነጉደዋል፡፤ እንደቀልድ ስምንት... Read more »
የሀገራችን የከፍተኛ ትምህርት፣ ቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ተቋማት ተማሪዎችን ከማስተማር ጎን ለጎን ጥናትና ምርምር በማድረግ እና ለኅብረተሰቡ ሥራ አጋዥ የሆኑ አዳዲስ ፈጠራዎች ጊዜ እና ጉልበትን የሚቆጥቡ ሥራዎች ይሠራሉ። ነገር ግን የሚወጡ ጥናትና ምርምሮች... Read more »
ህልሙን ያወቀ ሰው የቱ ጋር እንዳለ ያውቃል። ወዴት እንደሚሄድ ይረዳል። የሆነ ቀን ተነስቶ ‹‹እኔ በቃ እድሜዬ ዝም ብሎ አለፈ! ጊዚዬ ዝም ብሎ ነጎደ!›› አይልም። ወዴት እንደሚሄድ ያውቃል። መድረሻና መነሻውን ያውቃል። መንገዱን ጀምሮታል።... Read more »
የተወለዱባት ቀዬ እጅግ ነፋሻማ በተፈጥሮ የተዋበች መንደር ነበረች። በተራሮች የተከበበችው መንደር ብዙም ሰፊ የሚባል የእርሻ መሬት ባይኖርም ባለቻቸው መሬት ጥሩ ምርትን የሚያገኙ ገበሬ ቤተሰቦች መካከል ነበር ያደጉት። በቀየዋ በየቦታው የፈለቁት ምንጮች የአካባቢዋን... Read more »
ሉአላዊነት የአንድ ሀገር የክብር፣ የአይነኬ ስም ነው። እኛ መጠሪያ ስም እንዳለን ሁሉ የሀገራት የክብር ልኬት የልኡላዊነት ድንበራቸው ነው። ሁሉም ሀገራት በዚህ ስም በኩል ሀገርና ታሪክ ያቆዩ ናቸው። ይህ የክብር ስም የሀገር ባለአደራ... Read more »
ዓለም በማይገመት የቴክኖሎጂ ለውጥ አብዮት ውስጥ ይገኛል። የሰው ሠራሽ አስተውህሎ፣ የሮቦቲክስ ቴክኖሎጂ እና የበይነ-መረብ ቁሶች አዲስ የቴክኖሎጂ አብዮት እየፈጠሩ ነው። በተለይ የሰው ሠራሽ አስተውህሎ ብዙዎች ስለ ወደፊት እጣ ፈንታቸውና ሰብዓዊነት እንዲያስቡ ሳያደርጋቸው... Read more »
የለውጡ መንግሥት በሕዝብ ድምፅና ይሁንታ ኢትዮጵያን ማስተዳደር ከጀመረ እነሆ አራት ዓመት ሊሞላው ነው። በነዚህ ዓመታትም በተቻለው አቅም የሕዝቡን ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጥያቄዎችን ለመመለስ በርካታ ጥረቶችን ሲያደርግ ቆይቷል። በነዚህ አጭር ጊዜያት ውስጥ በተሠሩ... Read more »
ዘመናዊነት ከሚገለጽባቸውና የሥልጣኔ ማሳያ ተደርገው ከሚወሰዱ አበይት ክንዋኔዎች ውስጥ የከተማ ጽዱነት አንዱ ነው፡፡ ጽዳት ሕይወትና እድገት የተቆራኙበት የአንድ ወሳኝ ኩነት መጀመሪያና ማብቂያ ነው፡፡ በመርህ እና በአስገዳጅ ሕግ አይቀመጥ እንጂ ሁሉንም የሚያግባባ የጋራ... Read more »
መቼም ሀገራችን ከገባችበት ውጥንቅጥ ለመወጣት መፍትሄው በእጃችን ስለመሆኑ ማንም የሚጠፋው ያለ አይመሰለኝም። በዚህ ዘመን ‹‹አንተም ተው፤ አንተም ተው ብሎ›› የሚያስታርቅ ሽማግሌ ጠፍትቷል። አስታራቂ ሽማግሌ በታጣበት፤ አስታረቂ ጠፍቶ አራጋቢ አቀጣጣይ በበዛበት በዚህ ወቅት... Read more »
ኢትዮጵያ የነጻነትና የአይበገሬነት ተምሳሌት የመሆኗን ያህል፤ የጦርነት፣ የርሃብ፣ እርዛት፣ የመፈናቀልና የጥላቻ ትርክትን የያዙ ታሪኮችም ባለቤት ሆናም ትገለጻለች:: አብዛኛውን የኢትዮጵያን የውስጥ ታሪክ መለስ ብሎ ላየውም የውስጥ አለመግባባት፤ ግጭትና ጦርነት የበዛበት ነው:: በጋራ ታሪኮቻችን... Read more »