አዲስ ነገር ፈራን!

እውነታውን ማጤን የጀመርኩበትን ጊዜ ሳስብ ብዙ አጋጣሚዎቼን ታዘብኳቸው:: ከዕለታት በአንዱ ቀን ነበር… በመሃል አራዳ ጊዮርጊስ፣ በማዘጋጃ ቤት የቁልቁለት መንገድ ቁልቁል ወደ አቡነ ጴጥሮስ አደባባይ ማቆልቆል ጀመርኩኝ:: ድንገት ግን በጠራራው ፀሐይ ሰማዩ አለቀሰ::... Read more »

ሦስቱንም እንደ አንድ

በምናውቃቸው ነገሮች ውስጥ ሌላ የማናውቃቸው ብዙ ነገሮች ይኖራሉ፡፡ አንድ ብቻ የመሰለን ነገርን ብዙ ሆኖ ይሆናል፡፡ ብዙ ናቸው ብለን የምናስባቸው እልፍ ነገሮች ደግሞ አንድ ሆነው አሊያም እንደ አንድ ቆመው ልንመለከታቸው እንችላለን፡፡ በዚያን ሰሞን... Read more »

ከዓድዋ ድል በመማር ለቀጣይ ድል ራስን ማብቃት

ኢትዮጵያውያን የዛሬ 129 ዓመት ሊደበዝዝና ሊሻር የማይችል ነጻነታቸውንና ሉአላዊነታቸውን ያስጠበቀ ደማቅ ታሪክ ዓድዋ ላይ አስመዝግበዋል። ሀገራቸውን ቅኝ ሊገዛ የመጣውን የጣሊያን ሠራዊት ድል በማድረግ የተቀዳጁት ይህ ድል የሁሉም ኢትዮጵያዊ አሻራ ያረፈበትና በደማቁ የተጻፈ... Read more »

የዓድዋው የግጥም ምትሐት

ዓድዋ ሲወሳ የማይነሳ ስንኝ የለም:: በእናት ሀገር ጀንበር፣ በጦሩ አውድማ ሰላቶው ለመቃብር… በእሳት ለበሱ መድፍ ጎራዴ ዘምቶ፣ በስድስት ሰዓታት ውስጥ አፈር ከድሜ መብላቱ ምትሐት እንጂ ምን ሊሉት! ሳተናው አርበኛ በጠላት ሬሳ ላይ... Read more »

የብሌን አንዳች

በቢጫ የሽፋን ቀለም፣ ከጥቁር የሴት ምስል ጋር ፊቴ ድቅን ካለው መጽሐፍ ጋር ጥቂት ተፋጠጥኩ፡፡ ከመጽሐፉ አናት ላይ “የብሌን አንዳች” የሚል ርዕስ ውስጥ ፈርጠም! ብለው የቆሙት ፊደላት አንዳች ዓይን ይስባሉ፡፡ አንዳንዱም ከወገብ ሰበር!... Read more »

ሥነጽሁፍ ለሰላም ግንባታ

ሰውዬውን ገና ስመለከታቸው ነበር ለአዲስ አበባ ምድር እንግዳ መሆናቸውን የተረዳሁት። ክንብንባቸውን አውርደው ሰላምታ ሲሰጡኝ “ያውቁኛል?” አልኳቸው ያልለመድኩት ነገር ሆኖብኝ። “ምነው ጥላዬ? የሥላሴ ባሪያ አይደለህምን? እኛ በሀገራችን በኖርንበት ባሕል ከብቱ፣ አዝመራው፣ ዱር ገደሉን... Read more »

«ጀቢና» ከእውነት የተዘገነ ሕይወት …

ታላቅ የፈተና መንገድ፣ ሰፊ የጭንቅ ጎዳና፣ በሀዘን የሚሻገሩት፣ በችግር የሚያልፉት አስፈሪ የ|ሕይወት ድልድይ፡፡ በጸሀይና ጨለማ የተዋዛ፣ በደግ ክፉ የሚታገሉት ማንነት፡፡ ዕንባና ሳቅ ተዳብለው ፣ ታሪክ የወለዱበት፣ ጉልበት ከፍቅር ፣ መዋደድ – ከጥላቻ... Read more »

ኮሊውድ ላይ

ከቀናት በፊት ነበር አጋጣሚው:: እኔና ሁለት ወዳጆቼ ከአንደኛው ካፍቴሪያ ቁጭ ብለናል:: አብረን ቁጭ አልን እንጂ ለደቂቃዎች አብረን አልነበርንም:: በየፊናችን ስልክ ስልካችንን ነበር በዓይን የምናንተከትከው:: ድንገት ግን የአንደኛው ወዳጃችን መከረኛ ግርምትና የጩኸት ሳቁ... Read more »

በባከነች ክፍለ ጊዜ

በዩኒቨርሲቲው የስነ ጥበባት ክፍል መምህር የሆነው ዶክተር ጢሞቲዎስ፣ ከሰማይ ጠቀስ ቁመቱ የተነሳ ተማሪዎቹ ሁሉ “ጢሞ ሰንደቁ” እያሉ ነው የሚጠሩት። በግቢው ውስጥ ሁለት ለየት ያሉ ነገሮች አሉት፡፡ አንደኛውና የመጀመሪያው ነገር የዓመቱ የመጀመሪያው የትምህርት... Read more »

ከገጸ ሰብ ባህር

ምድራችን ከተሸከመቻቸው እጅግ ግዙፍና ጥልቅ ባህሮች የገዘፈው ባህር የት ነው ካልን የትም ሳንሄድ እኛው ውስጥ ነው። ከሰውነት ክፍሎቻችን መካከል ባህርን የመሰለ ባህሪ ያለው ከራስ ቅላችን ላይ የሰፈረው አዕምሯችን ነው። የገጸ ሰብ ባህረ... Read more »