ፍቅር ጌታ

ፀሐይ ውበታም ሴት ናት፡፡ ተፈጥሮ የአንዲትን ውብ ሴት ፈገግታ ፀሐይ አድርጎ ህዋ ላይ የሰቀላት ይመስለኛል፡፡ ዓለም የደመቀችው በፀሐይ በተሳለችው የሴት ልጅ ፈገግታ ነው፡፡ እሷን ሳይ እንዲህ ብቻ ነው የማስበው፡፡ የምሠራበት ቦታ ሰርቪስ... Read more »

ሴትና ሴት

መጀመሪያ ያየኋት ከእናቷ ጋር ነው.. እሷን ከምትመስል መልከኛ እናቷ ጋር፡፡ ከሴት የተወዳጀ ሴትነት መልኩን በእሷ ነው ያየሁት፡፡ ከእናት የተወዳጀ ሴትነት ከአባት እንደተወዳጀ ወንድነት ይሆን? በትልቅነት የእናትን ክንድ ተደግፎ በጠዋት ከእንቅልፍ መንቃት፣ የዓለምን... Read more »

በጎነት የነፍስ ወለባ

ብቻውን ሲሆን ወደተወው ትላንትና ነው የሚሄደው። በሀሳብ ሽምጥ ይጋልባል። ያደገው ከአባቱ ጋር ነው..እንደዛች መቀነቷን ፈታ ያላትን አንድ ሳንቲም እንደጣለችው ድሃ እመበለት ካለው ላይ እየቆረሰ ከሚሰጥ አባቱ ጋር። ሕይወት ማለት ለሌሎች መኖር ነው፣... Read more »

 ከሴቶች ሁሉ የተለየች

 መልኳን እፈራዋለው..ሴትነቷ ያስደነብረኛል። ማለዳ የትካዜዋ መነሻ እንደሆነ በደጇ በማገድምበት ጠዋት አስተውያለሁ፡፡ ጀምበርን ተከትሎ የምትወድቅበት ትካዜ አላት፡፡ ከማለዳ ፈቀቅ ባለ የሆነ ጠዋት ላይ ስብር..ስብርብር ትላለች። ብዙ ነገሯ ያስኮበልለኛል፡፡ እሷ ባለችበት ደጅ ሳገድም በጥያቄ... Read more »

ፈተና እና ፍርቱና

እግዜር ነፍስ በሚሏት ብናኝ ሕይወትን ሲሰራ ሃምሳ እጅ ፈተና ሃምሳ እጅ ፍርቱናን ተጠቅሟል እላለሁ፡፡ ብዙ ባልኖርኩት የዘመን ሚዛን ላይ ሕይወትን ስመዝናት ይሄን እውነት ነው ያገኘሁት። ለዛም ነው በሳቃችን ማግስት የምናለቅሰው፡፡ ለዛም ነው... Read more »

 ድርና ማግ

ተፈጥሮዋ እንደ ጀምበር ነው። ዝም ብላ የምትደምቅ። የምትፋጅ። ቀይ ናት፤ እንደ ጀምበር። ቀና ያለን ሁሉ የሚረመርም እሳታማ ውበት አላት። ሳያት የጀምበር መሀሉን፤ ከዋክብቶች ያደመቁትን ብራ ሰማይ ትመስለኛለች። ሳያት ክረምት ያለመለመው ጠልና ጤዛ... Read more »

 የነፍሴ ሁለት ሴት

ልባም ሴት ሁለት ቦታ ትፈጠራለች ‹ምድር ላይ እና በባሏ ልብ ውስጥ› የሚል ከማን እንዳገኘሁት የማላውቀው የልጅነት እውቀት አለኝ። ልክ እንደ ርብቃ አንዳንድ ሴቶች ብዙ ናቸው.. እልፍ መዓት። በወንድ ነፍስ ውስጥ የትም የሚገኙ..።... Read more »

 ባትመጪም ቅጠሪኝ

ቀጠሮ ማክበር አይሆንላትም። ማንም የሚቀድማት ሴት ናት። ኖራ ኖራ ሰዓት የሚያጥራት ለቀጠሮ ነው። አልመሽ ያላት ቀን፣ በእርዝመቱ ሁሌም የምትረግመው እሁድ እንኳን ቀጠሮ ያላት ቀን አይበቃትም። ቀጠሮ ያላት ቀን ማንም የሚቀድማት ሴት ናት።... Read more »

ድሮና ዘንድሮ

ነፍስ ድሮና ዘንድሮ ብራናና ወናፍ ናት..አንድ ዓይነት መስላ የተለየች። እንደ ጊዜ የሰው ልጅ ሠርግና ሞት የለውም። ከመኖር ወደአለመኖር ይወስደናል። ካለመኖር ወደመኖር ይመልሰናል። እናም ጊዜ አለቃ ነው..ትላለች የጠየፋት ራሷ በታወሳት ቁጥር። ጊዜን ታኮ፣... Read more »

በፍቅር ስም

ኮማንደር እንዳሻው ከአዳራሹ ሲወጣ ቀይዳማ ፊቱ ገርጥቶ ነበር፡፡ የቢሮውን በር ከፍቶ ከመግባቱ ስልኩ አንቃረረ፡፡ ከንዴቱም ከድካሙም ገና አላገገመም ነበር፡፡ ማረፍ ፈልጓል፣ መረጋጋትም..እና ደግሞ በጽሞና ማሰብ፡፡ ቢሮ ሲገባ ከራሱ ጋር ሊያወራ ፕሮግራም ይዞ... Read more »