
ብስራት በተለያየ መልከኛ እርሳሶች ስዕል እየሳለ አባቱ ፊት ይንደፋደፋል። አጠገቡ አብሮት የሚጫወተው የፈረንጅ ውሻ ዝም ብለህ ተቀመጥ የተባለ ይመስል የብስራትን ድርጊት በተመስጦ ያስተውላል። የብስራት አባት ጋሽ ተፈራ ርዕሱ የተሸፈነ መጽሐፍ እያነበቡ ከብስራትና... Read more »

ከእናቱ ጋር ጎን ለጎን ቁጭ ብሏል። እድሜ ድሩን አድርቶባቸው እናቱን ወደ እርጅና እሱን ደግሞ ወደ ጉልምስና ወስዷቸዋል። የእናቱ አዛውንት እጅ እንደ ልጅነት ጊዜው ከበራ ጭንቅላቱ ላይ ሊወጣ ሲታከከው ይታየዋል። ‹አይ እማ! ዛሬም... Read more »
ታክሲ ውስጥ ነው፤ ወደ ሃያ ሁለት እየሄደ፣ ፊቱን ወደ ግራ አዙሮ በመስተዋቱ ውስጥ ወደ ውጪ ያስተውላል፤ አዲሳባን እያየ:: ቆነጃጅቷን፣ ጉዷን፣ ትናንቱን ዛሬውን ሳይቀር ተመለከተ:: ሁሉንም ነገር ልብ ብሎ ማየት ይወዳል፤ በተለይ ቆንጆ፤... Read more »
ኢትዮጵያ መልኮች አሏት፤ ገነትን እንደሚከቡ አራቱ ወንዞች ዘላለማዊ ቁንጅናን የታጠቁ። የኢትዮጵያ መልኮች እግዚአብሄራዊ መልኮች ናቸው፤ በመስጠት የከበሩ። ስይጥንናን የማያውቁ ብርሀናማ መልኮች። እንዲህ ስታስብ የአያቷ ድምጽ ከውጪ ተሰማት። ‹እግዚኦ..እግዚኦ.. ‹ምነው እማማ ተዋቡ? ጋሽ... Read more »

‹ዝናቡ..አንተ ዝናቡ? እማማ ሸጌ ተጣሩ። እጃቸውን በአዳፋ ቀሚሳቸው እየጠራረጉ። ‹እማማ ሸጌ! ዝናቡ አይበሉኝ..ስሜ ሸጋው ነው..እርሶ ትልቅ ሰው አይደሉ? ባኮረፈ ድምጽ። ‹ምን እኔ ላይ ዘራፍ ትላለህ! ያወጡልህ ጓደኞችህን እነሱን ሀይ አትልም ነበር›። ‹በቃ... Read more »

ወደ ክፍለ አገር እየሄድኩ አውቶቡስ ውስጥ ቁጭ ብያለሁ። በእድሜ ተዋረድ የተሳሉ አያሌ ነፍሶች ሽንጠ ረጅሙን አውቶቡስ ሞልተውታል። ካለፈለፈ የሚያመው የሚመስለው አንድ ወያላ ለግብዣ በተመቸ ድምጽ ተሳፋሪ ይጣራል። ሀዋሳ…ሻሸመኔ እያለ። ጸጉሩን እየቆነደደ፣ እጁን... Read more »

አባቴ የሕይወት ዘመኔ ያልተመለሰ ጥያቄዬ ነው፣ አድጌ እንኳን ሮጬ ያልደረስኩበት ከፍታዬ ነው። እዚህ ምድር ላይ ሮጬ ያልደረስኩበት አባቴና ሀሳቡ ናቸው። ሀሳቡ ይገርመኛል፤ ድሆች የሌሉበት የባለጸጋ ሀሳብ የለውም። አባቴ ሁልጊዜ ከድሆች ርካሽ ዕቃዎችን... Read more »
እሌኒን እየጠበቅሁ ፒያሳ ቁጭ ብያለሁ፤ እንደ ዛሬ ሰው ለማግኘት ተስገብግቤ አላውቅም። ጓደኛዬ ቶማስ የመጀመሪያ ቀጠሮ ላይ ጥሩ ሆኖ መገኘት ዋጋ አለው ስላለኝ ጥሩ ሆኜ ለመታየት ያላደረኩት የለም። ጸጉሬን ከተማው ውስጥ አለ የተባለ... Read more »

ሴትና አገር፤ አገርና ሴት ከአንድ ወንዝ የተቀዱ ይመስሉኛል። በአገር ውስጥ ሴትነት፣ በሴትነት ውስጥ አገር ጥዑም ዜማ ናቸው። በአገር ውስጥ ሴት ቅኔ ናት፣ በሴትነት ውስጥ አገር ዜማ ናት። በተለይ ሄለንን ሳይ ይሄ ሀሳቤ... Read more »
ሁሌ ጠዋትና ማታ በታሰርኩባት ጠባብ ክፍል መስኮት አጠገብ ቆሜ አባቴንና ሙሴን አስታውሳለሁ። አባቴ መምህር እንድሆንለት ነበር ፍላጎቱ፤ ለመምህርነት ልዩ ፍቅር ነበረው። ሁሌ በገባሁ በወጣሁ ቁጥር አንተ መምህር ነህ፤ ስትራመድ ይሄን እያሰብክ ተራመድ... Read more »