ምድር በረፋዷ ጀምበር ረስርሳለች። ለጸሀይ መውጫ ደረቱን የሰጠው መኝታ ክፍሏ በረፋዷ ጀምበር ግንባር ግንባሩን እየተባለ ቆሟል። መስተዋቱ ላይ ያረፈው የጸሀይዋ ብርሀን ወደ ክፍሉ ተንጸባርቆ ጨለማ ክፍሏን በጠይም ውጋግ ሞልቶታል። ተኝታለች..አተኛኘቷ ፍትወት ይቀሰቅሳል።... Read more »
በተቀመጠበት ትንሽዬ ክፍል ውስጥ የሰኔ ገመገም ይሰማዋል። ጥቁር ደመና ያረገዘ ነፍሰ ጡር ሰማይ በገርባባ በሩ በኩል ያላግጥበታል። ጭር ያለ ጅብማ ዓለም ዝናብን ሊወልድ ከሚያምጥ ሰኔ ጋር አብሮ ያሾፍበታል። ግንቦት አልፎ የሚመጣው ወር... Read more »

የህይወት ውበት ትዝታና ተስፋ ናቸው። ነፍስ በትዝታና በተስፋ መርፌ የተሰፋች ይመስለኛል። ደግሞም ተሰፍታለች፣ ከጠዋት እስከ ማታ የማረምመው አርምሞ የነፍስ ባለቀለም እንጉርጉሮ ከመሆን ሌላ ምን ሊሆን ይችላል? ህይወት ከፊት ትዝታ ከኋላ ተስፋ ባይኖራት... Read more »
ራሴ የጠፋብኝ ሰው ነኝ..ራሴን ካጣሁት ሰንብቻለው:: ማነህ ላለኝ ማቲያስ ነኝ እላለው እንጂ ማቲያስ ማን እንደሆነ አላውቀውም:: ሰው እንዴት ራሱ ይጠፋዋል? ስል እኔው በኔ እደነቃለው:: ሰው ራሱን አጥቶ ምንም ቢያገኝ እንደማይረካ አንድ ማለዳ... Read more »
አስናቀ ለረጅም ሰዓት እያነበበ ከተቀመጠበት ቦታ ላይ የመነጠቀው የስልኩ ጥሪ ነበር።የሚያነበውን መጽሐፍ ገታ አድርጎ ወደ ስልኩ ሲያስተውል የጓደኛው የናሆም ስምና ቁጥር ስልኩ ስክሪን ላይ እየቦረቀ አገኘው። ስድስት ሰዓት አለፍ ሲል ሁሌ ይደውልለታል።... Read more »

ስራ ስትገባና ከስራ ስትወጣ አይኖቿ አንድ ሰው ላይ ማረፋቸው ግድ ነበር። የመስሪያ ቤታቸውን ሽንጠ ረጅም አጥር ተደግፎ የሚኖር አንድ ሰውን። ይህ ሰው በህይወቷ አብዝታ ያየችው ሰው ነው። ነፍሷ ብትጠየቅ እንደዚህ ሰው ፊት... Read more »

ከገነት ስፍራዎች አንዱን የሚመስል፣ የመላዕክት ስውር ሹክሹክታና ጽሞና የሚደመጥበት ከሰባቱ ሰማያት አንዱን የወረሰ፣ በአይን እየገባ ከነፍስ የሚያርፍ በደስታ እቅል የሚያሳጣ ቦታ፣ ነጭ አረፋውን እየደፈቀ በጌጣም ድንጋዮች ላይ የሚቦርቅ ፏፏቴ፣ እንደ ገረገራ በረድፍ... Read more »

የሰፈራችን እድር ለፋፊ ጋሽ ቢራራ ትላንት ማለዳ ለአባቴ እንድነግረው መልዕክት ልከውኝ ነበር። ዛሬ ጠዋት መንገድ አግኝተውኝ “ለአባትህ ነገርከው እንዴ” ቢሉኝ ነው ስበር ቤት የመጣሁት። ቤት ስገባ አባቴ ዜና እያደመጠ ነበር። በእኛ ቤት... Read more »

ከእንቅልፏ ነቅታ ስልኳን ስታየው ማቲ አራት ጊዜ ደውሎ ነበር። ከዚህ በፊት እንዲህ እንደ አሁኑ በጠዋቱ ነቅታ ስልኳን ስታየው የምታውቀውም የማታውቀውም ብዙ ስልክ ተደውሎ ነበር የሚጠብቃት። አሁን ከማቲ በቀር ማንም የሚደውልላት የለም። እነዛ... Read more »

ያረፍዳል.. አንድም ቀን በሰዓቱ ክፍል ገብቶ አያውቅም። ከመምህር እስከ ተማሪ በእሱ ኋላ መቅረት ብዙዎች ተዘባብተዋል። ‹ቆይ አንተ ስንት ሰዓት ከእንቅልፍህ ብትነሳ ነው ከተማሪ መጨረሻ ክፍል የምትደርሰው› ሲሉ ጓደኞቹ ስቀውበት ያውቃሉ። ማርፈድ የስንፍና... Read more »