በዕድሜ አልያም በተለያዩ ፅኑ ህመሞች ሕክምና ሲደረግ ቆይቶ ከሚከሰት የህልፈተ ሕይወትና የአካል ጉዳት ውጪ ሩጫቸውን ሳይጨርሱ አንዳንዴም ገና ሳይጀምሩ በጨቅላ ዕድሜያቸው የሚቀጩ እንዳሉ ማድመጥ በዕለት ተዕለት እንቅስቃሴ ውስጥ የሚያጋጥም ነው። ለዚህ አንዱ መንስኤ ደግሞ የሕክምና ስህተት ነው። የቀላል ራስ ምታት ምክንያታቸውን
ለማወቅ ወደ ሐኪም ቤት አቅንተው ‹‹ምነው እግሬን በሰበረው›› የሚያስብሉ የአካል ጉዳቶች ከፍ ሲልም እስከ ህልፈተ ሕይወት የሚደርስ አደጋ እንደሚያጋጥም ሲነሳ ይደመጣል፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ ልዩ ስሙ አቧሬ አካባቢ ነዋሪ አቶ ወንድወሰን አዝብጤም የችግሩ ሰለባ መሆናቸውን ከዓይናቸው ልውረድ አልውረድ የሚል እንባቸው ጋር ትንቅንቅ ፈጥረው ገለጹልን፡፡
አቶ ወንድወሰን ከዓመት በፊት በሁለቱም እጃቸው ላይ ለወጣባቸው እባጭ መፍትሔ ለማግኘት ወደ የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ ማምራታቸውን አስታውሰዋል፡፡ በወቅቱም ሐኪም ከተመለከታቸው በኋላ የባሰበት የግራ እጃቸው በመሆኑ ቅድሚያ የቀዶ ጥገናው ይኸው እጃቸው ይደረጋል፡፡ ቀዶ ጥገናውም በጥሩ ሁኔታ በመጠናቀቁ ከዓመት ቀጠሮ በኋላ ሲመጡ በሌላ ሐኪም የቀኝ እጃቸው ይሠራላቸዋል፡፡ ሕክምናውን የሰጠቻቸው ሐኪም ቀላል ቀዶ ጥገና እንደሚሰጣቸው ስትገልጽላቸውም ከዚህ ቀደም ተኝተው መታከማቸውንና ለ26 ዓመታት የስኳር ሕመምተኛ እንደሆኑ ሊያስረዷት ይሞክራሉ። ይሁን እንጂ በማግስቱ እንዲሠራላቸው በመወሰኑ ታህሳስ 3 ቀን 2011 ዓ.ም ከጠዋቱ ሦስት ሰዓት ከሩብ የገቡ ስምንት ሰዓት ሊሆን ሲል መውጣታቸውንም ነው የተናገሩት፡፡ ቀዶ ጥገና የተደረገበት ቀን ጨምሮም ሁለት ቀን ድንገተኛ ክፍል ገብተው ነበር፡፡
ቀዶ ጥገናው ከተጠናቀቀ በኋላም በሦስተኛው ቀን ወደ ጤና ጣቢያ ሄደው ፋሻ እንዲያስቀይሩ መላካቸውንም አቶ ወንድወሰን አስታውሰዋል። በተባሉበት ዕለት ወደ ጤና ጣቢያ ሲያመሩም በቅድሚያ ሐኪሙ ዓይቶት እንደሚፈታ ተገልፆላቸው ተመልሰዋል፡፡ የካቲት 12 ሆስፒታል በማቅናትም የሕክምና ባለሙያዎችን ሲያናግሩ ተመሳሳይ ምላሽ አግኝተዋል፡፡ ቀዶ ጥገናውን ወደ ሠራቻቸው ሐኪም በመሄድ ያጋጠማቸውን ቢነግሯትም ጤና ጣቢያ ይህን የመሥራት ግዴታ አለባቸው በማለት ልታስተናግዳቸው ፈቃደኛ እንዳልሆነች ነው የገለጹት፡፡
‹‹ምንም እንኳ ሕመሙ እኔ ጋር ቢሆንም ሞያው ግን የሕክምና ባለሞያዋ ጋር ነው›› በማለት ዕምነት የጣሉባት ሐኪም ያደረገችላቸው ሕክምና ቆዳቸውን በመግፈፍ ይብሱን ጣቶቻቸው እንዳይታጠፉና እንዳይዘረጉ ብሎም እንዲሸበሸብ እንዳደረጋቸው ተናግረዋል፡፡ ቀድሞ በሹፍርና ሥራ የዕለት ጉርሳቸውን ይበሉበት የነበረ እጃቸው በአሁኑ ወቅት ከሥራ ውጪ ሆኗል፡፡ ስለ ጉዳዩ ሊያናግሯት ቢሞክሩም አጥጋቢ ምላሽን አላገኙም።
ለበላይ አካል ቅሬታ ማቅረባቸው ተገቢ እንዳልሆነና እንዲተውት ከሌሎች የተቋሙ የሕክምና ባለሙያዎች ጋር በመሆን በር ዘግታ እንዳናገረቻቸውም አቶ ወንድወሰን ተናግረዋል። መፍትሔ እስኪያገኙ አቤቱታቸውን ማሰማት እንደማያቆሙ በመናገራቸውም በተቋሙ ተገቢውን አገልግሎት እንኳ ሊያገኙ እንዳልቻሉ ነው በምሬት የገለጹት፡፡ ከዚህ የከፋ ብዙ ፈተናም በታካሚዎች ላይ እንደሚደርስ በመጠቆም፤ በርካቶች ወዴት እንደሚኬድ ባለማወቅ ችግራቸውን ይዘው ይቀመጣሉና መንግሥት የጤና ተቋማትን ቢፈትሽ ሲሉ ጠይቀዋል፡፡
በየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ ዋና ፕሮቮስት ዶክተር አየለ ተሾመ፤ ተገልጋዩ ቢሯቸው በመሄድ ቅሬታቸውን በቃል ማቅረባቸውን ቢያምኑም ቅሬታቸው ግን የተደበላለቀ ነው ብለዋል፡፡ ከቀዶ ጥገናው በኋላ እጃቸው አለመዳኑን በቅሬታነት የሚያነሱ ሲሆን፤ ለዚህ እንደ ማሳያ የሚያቀርቡት ሌላኛው እጃቸው ተመሳሳይ ሕክምና ተደርጎለት በቶሎ መዳኑን ነው። ተመሳሳይ ቀዶ ጥገና ከዚህ በፊት በጥሩ ሁኔታ ተደረገ ማለት በሌላ ወቅት ለሚደረግ ቀዶ ጥገና በሠላም መጠናቀቅ ዋስትና ሊሆን አይችልም። ውጤታማ አልሆነም ማለት ሐኪሙ ስህተት ፈጥሯል ማለትም አይደለም ይላሉ፡፡
ቁስሉ በፍጥነት ካልዳነ የሕክምና ባለሙያው ተከታትሎ በድጋሚም ቀዶ ጥገና ሊደረግ ይችላል። ሁሉም ክትትል የሚደረገው ግን ቀዶ ጥገና በተደረገበት ተቋም ላይሆን ይችላል። ቁስሉን ለማስጠረግ በአቅራቢያ በሚገኝ ጤና ጣቢያም ሊሄዱ ይችላሉ። ነገር ግን ጤና ጣቢያዎች አንዳንዴ በሆስፒታል የተጀመረ ሕክምና በዚያው ማለቅ አለበት የሚል ምላሽ ይሰጣሉ። ይህን ያመጣውም የአገልግሎት አሰጣጥ ላይ ያሉ ክፍተቶችና የቅብብሎሽ ሥርዓቱ ድክመት ነው። ከዚህ ውጪም ተገልጋዮችን እንደ ግንዛቤ ደረጃቸው ማነጋገር ላይ የሚስተዋሉ ክፍተቶችም የቅሬታ መነሻ ሲሆኑም ይስተዋላል፡፡
ተገልጋዩ አቤቱታቸውን ካሰሙ በኋላ በአግባቡ አገልግሎት ሊሰጣቸው አለመቻሉን ማንሳታቸውን ዋና ፕሮቮስቱ ገልፀዋል፡፡ ችግሩን ለመፍታት የሕክምና ባለሙያዎችን የማነጋገር ሥራ ተሠርቷል። ተገልጋዮች ሕመማቸው ከሚፈጥርባቸው የጤና መጓደል በተጨማሪ ብዙ ዓይነት ባህርይን ሊያሳዩ እንደሚችሉ በመገንዘብ ሐኪሞች በሠከነ አዕምሮ የመቀበል ኃላፊነት እንደሚኖርባቸውም አምነዋል፡፡
ሌላኛው ቅሬታ የሕክምና ስህተት ተፈጥሯል የሚል በመሆኑ ይህንንም ለማጥራት ተሞክሯል። ግለሰቡ 30 በሚጠጉ ዓመታት የስኳር ሕመምተኛ መሆናቸውን በማንሳት ይህም ቶሎ ቁስል እንዳይድን በሽታ የመከላከል አቅም ማነስ የሚያስከትል በመሆኑ እንደሌሎች ሰዎች ሁሉ ቀዶ ጥገና ሠላማዊ እንዳይሆን ሊያደርግ ይችላል። በማጥራቱም በተረጋገጠው መሠረት ምንም ዓይነት የሕክምና ችግር የለም በማለት ባለጉዳዩ ያነሱትን ቅሬታ አስተባብለዋል፡፡ ነገር ግን ተገልጋዩ አሁንም ችግር እንደገጠማቸው ካመኑ ቅሬታዎችን ለሚመለከተው የሕክምና አገልግሎት አሰጣጥ የሥነምግባር ኮሚቴ በጽሑፍ ሊያቀርቡ እንደሚችሉ ዋና ፕሮቮስቱ አስታውቀዋል፡፡
ቅሬታዎችን የሚመለከተው ኮሚቴ ገለልተኝነትስ የሚለውን ጉዳይ አስመልክቶ ዶከተር አየለ፤ ውስጣዊ ኮሚቴው ከወገንተኝነት ሙሉ በሙሉ የፀዳ ነው የሚል ማረጋገጫ መስጠት አዳጋች ቢሆንም የኮሚቴውን ውሳኔ ከመቀበል ይልቅ ሚዛን ላይ አስቀምጦ መመልከት የተቋሙ የበላይ አስተዳደር ኃላፊነት በመሆኑ በየደረጃው እንደሚታይ አካሄዱን አብራርተዋል፡፡ ይህ አጥጋቢ ካልሆነም ገለልተኛ ወደሆኑ ተቋሞች በመሄድ አቤቱታ ማሰማት የሚቻልበት አሠራር ምቹ ነው፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የምግብ፣ መድሐኒት፣ ጤናና እንክብካቤ አስተዳደርና ቁጥጥር ባለሥልጣን የሕግ አገልግሎት ክፍል ኃላፊ ወይዘሮ ዱሬ ዘላለም፤ ከግለሰቦች፣ ከፍርድ ቤት፣ ከዐቃቤ ሕግና ከፖሊስ ጣቢያ የሕክምና ስህተት ተፈጥሯልና ይጣራ በሚሉ አቤቱታዎች ወደ ባለሥልጣኑ እንደሚደርሱ ገልፀዋል፡፡ ባለፉት ሦስት ዓመታትም ከዚህ ጋር የተያያዙ 161 ቅሬታዎች ቀርበዋል፡፡ ከዚህ ውስጥ ቅሬታው ትክክለኛ ሆኖ ተጠያቂ የተደረጉ፣ በነፃ የተለቀቁም እንዲሁም በመታየት ላይ ያለና ውሳኔ ያላረፈባቸው ጉዳዮችም አሉ፡፡
የተሰጠው ውሳኔ ዓይነትም ከፍተኛ ከሆነው ለአንድ ዓመት ከአምስት ወር የሞያ ፍቃድ እገዳ ጀምሮ የሕክምና ሞያ ፍቃድ ሙሉ በሙሉ እስከ መሠረዝ ይደርሳል፡፡ ለባለሥልጣኑ የሚቀርቡ ቅሬታዎች የሚጣሩት ከሕክምና ሞያ የተውጣጡ ሐኪሞች፣ ከምክር ቤት ሁለት ሰዎች እንዲሁም ከሕግ ባለሙያዎች ባቀፈ ኮሚቴ ነው፡፡ ኮሚቴው ከሚያሳርፈው አስተዳደራዊ ውሳኔ ጎን ለጎን በፍርድ ቤት ደግሞ የፍትሐ ብሔርና የወንጀል ተጠያቂነቱ ይኖራል፡፡
ወደ ባለሥልጣኑ ከሚመጡት ቅሬታዎች መካከል በብዛት የአካል ጉዳት ሲሆን፤ ሕልፈተ ሕይወትም እንዳለ ነው ኃላፊዋ የተናገሩት፡፡ በተለይም የእናትና የጨቅላ ሕፃናት ሞት ይጠቀ ሳል፡፡ ችግሮቹ ከሚፈጠሩባቸው ምክንያቶች ውስጥ የሞያ ብቃት ማነስ አንዱ ቢሆንም ዋነኛው ግን በቸልተኝነት የሚመጣ ችግር እንደሆነ ማረጋገጥ ተችሏል። ችግሮቹን ለማቃለልም ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን በየጊዜው የንቅናቄ መድረኮች ይዘጋጃሉ።
ኃላፊዋ እንደሚሉት፤ ባለሥልጣኑ ከተለያዩ ተቋማት ጋር በመሥራት ለሆስፒታሎች፣ ለጤና ጣቢያዎች ብሎም ለግልም ሆነ ለመንግሥት የጤና ተቋማት ሥልጠናዎችን እየሠጠ ይገኛል። በዚህ ደረጃ ቅሬታዎችን ማቅረብ የሚቻልበት አሠራር እንዳለ ግንዛቤ ክፍተት እንዳለ በመግለጽም፤ በቀጣይ ተገልጋዮች በሕክምና ስህተት እንደተፈጠረባቸው ሲያምኑና መሠል ችግሮች ሲያጋጥም ወደ ባለሥልጣኑ ቀርበው ቅሬታቸውን ማስገባት እንደሚችሉም አስታውቀዋል።
አዲስ ዘመን መጋቢት 9 /2011 ዓ.ም
ፍዮሪ ተወልደ
For the reason that the admin of this site is working, no uncertainty very quickly it will be renowned, due to its quality contents.
Профессиональный сервисный центр по ремонту бытовой техники с выездом на дом.
Мы предлагаем: ремонт крупногабаритной техники в москве
Наши мастера оперативно устранят неисправности вашего устройства в сервисе или с выездом на дом!
Профессиональный сервисный центр по ремонту компьютероной техники в Москве.
Мы предлагаем: ремонт системного блока
Наши мастера оперативно устранят неисправности вашего устройства в сервисе или с выездом на дом!
Профессиональный сервисный центр по ремонту фото техники от зеркальных до цифровых фотоаппаратов.
Мы предлагаем: ремонт видеопроекторов
Наши мастера оперативно устранят неисправности вашего устройства в сервисе или с выездом на дом!
Если кто ищет место, где можно выгодно купить раковины и ванны, рекомендую один интернет-магазин, который недавно открыл для себя. Они предлагают большой выбор сантехники и аксессуаров для ванной комнаты. Ассортимент включает различные модели, так что можно подобрать под любой стиль и размер помещения.
Мне нужно было раковина в ванну , и они предложили несколько отличных вариантов. Цены приятно удивили, а качество товаров на высшем уровне. Также понравилось, что они предлагают услуги профессиональной установки. Доставка была быстрой, и всё прошло гладко. Теперь моя ванная комната выглядит просто великолепно!
ремонт бытовой техники самара
<a href=”https://remont-kondicionerov-wik.ru”>профессиональный ремонт кондиционеров</a>
Профессиональный сервисный центр по ремонту компьютероной техники в Москве.
Мы предлагаем: ремонт компьютеров на дому в москве
Наши мастера оперативно устранят неисправности вашего устройства в сервисе или с выездом на дом!
Профессиональный сервисный центр по ремонту бытовой техники с выездом на дом.
Мы предлагаем: сервисные центры в нижнем новгороде
Наши мастера оперативно устранят неисправности вашего устройства в сервисе или с выездом на дом!
Профессиональный сервисный центр по ремонту бытовой техники с выездом на дом.
Мы предлагаем: ремонт бытовой техники в перми
Наши мастера оперативно устранят неисправности вашего устройства в сервисе или с выездом на дом!