አረንጓዴ አስተሳሰብ አረንጓዴ ትውልድ ከሚፈጥሩ በጎ እሳቤዎች ውስጥ ቀዳሚው ነው። የተፈጥሮ መልካችን በራስ ወዳድነት ወይቦ ቀለሙን ስቷል። አረንጓዴ ዐሻራ የሌለው ተግባራችን ህልውናችንን ጥያቄ ውስጥ ከከተተው ቆይቷል። በሥልጣኔአችን ውስጥ ነገን ረስተን ስለአሁን ብቻ በማሰብ በእኩይ ስራችን ተፈጥሮን ወደመርዝነት እየቀየርናት ነው። አይደለም ለመጪው ትውልድ ለእኛ እንዳትሆን የስጋት ካባን ደርበንባታል።
custom nfl jersey
cheapest customized t shirts
custom basketball jerseys
custom jerseys soccer
custom jersey
team jerseys
custom football jerseys
custom jersey basketball
custom hockey jersey
all nfl jerseys
custom jerseys online
custom nfl jerseys
custom design
custom nba jerseys
cheap jerseys custom
customize football jersey
baseball jerseys custom
cheap jerseys online
nfl custom jerseys
custom soccer jerseys
custom jerseys online
custom hoodies cheap
custom jersey maker
customize jersey soccer
custom basketball
custom softball jerseys
custom basketball jerseys
customize jersey basketball
custom jerseys
cheap jerseys
custom football uniforms
jersey store
cheap football jerseys
custom jersey maker
custom jerseys
cheap jerseys
custom basketball jerseys
nba jersey customized
custom soccer jersey
custom baseball jerseys
custom soccer jerseys
ትውልድ በአስተሳሰብ ነው የሚፈጠረው። አስተሳሰቡ መልካም የሆነ መሪና ህዝብ በሃሳቡ በኩል ራሱን ያየዋል። የሃሳብ እድፍ በብዙ ነገር የተራቆተ ትውልድና ሀገር ይፈጥራል። እስኪ ዛሬ ላይ ሆነን ራሳችንን እንፈትሽ በሃሳባችን ውስጥ ምን አለ? እራስ ወዳድነት ፣ ዘረኝነት፣ አክራሪነት … ። ከጉዳይህ ወጣህ እንዳትሉኝ..ከጉዳዬ አልወጣሁም። እዛና እዚህ የምረግጠው የሳትነውን ካልሳትነው ጋር ለማያያዝ ነው።
ጉዳዬ አረንጓዴ አስተሳሰብ ለአረንጓዴ ትውልድ ነው። አስተሳሰብ የሁሉም ነገር መሠረት ነው። ዛሬ ላይ በአረንጓዴ አስተሳሰብ አረንጓዴ ትውልድና ምድር ለመፍጠር የምናደርገው ጥረት ነገ ላይ ለተፈጥሮ የቀረበና የቀና ትውልድ ለመፍጠር ትልቅ አቅም እንደሚሆነን ይታመናል። ተፈጥሮ መልኳ አረንጓዴ ነው። የተፈጥሮ ማህጸን አረንጓዴን ወልዶ እንዲያሳድግ በተፈጥሮ አስገዳጅነት የጸና ነው። ሰማይ ሰማያዊ ምድር አረንጓዴ ሆነው የተፈጠሩበት የራሳቸው ምክንያት አለ። ምድርና የሰው ልጅ ህልውናቸውን የሚያስቀጥሉት በተፈጥሮ እውነት በአረንጓዴ ቀለም ውስጥ ሲቆሙ እንደሆነ ወደሰማይ ቀና ስንል ወደምድር ዝቅ ስንል የምናየው ሀቅ ነው።
እንደሰው ልጅ ተፈጥሮን የሻረ፣ ሥርዓትን የተዳፈረ የለም። እየሞትንና እየተጎሳቆልን ያለነው በእንዲህ አይነቱ የሥርዓት ሽረት ነው። የመኖር ዋስትናችን የሚረጋገጠው በአረንጓዴ አስተሳሰብ አዲስ ምድርና አዲስ ትውልድ ስንፈጥር ነው። በገዛ እጃችን ያራቆትነውን ምድር በገዛ እጃችን እስካላለበስን ድረስ በገዛ እጃችን ሞትን መርጠናል ማለት ነው።
ሞትን መምረጥ መሸነፍ ነው። ሰው ለችግሩ መፍትሄ የሚሆን ሃሳብና መላ ሲፈጥር ነው የሚጀግነው። ልክ እንደዚህ አረንጓዴ አስተሳሰብ የሰውን ልጅ ሁሉ ከሞት የሚታደግ እሳቤ ነው። ዓለም እየሞተች ያለችው በአየር ንብረት ለውጥ ሳቢያ እንደሆነ የቆየ እውቀት አለን። የአየር ንብረት ለውጥ ደግሞ ከአረንጓዴ እሳቤ ያፈነገጠ ሥልጣኔና ዘመናዊነት አብረው የፈጠሩት የራስወዳድነት ውጤት ነው። ከትናንት ወደዛሬ የመጣ ወደነገም ሊሄድ የሚያኮበኩብ የሥልጣኔ ልክፍት። የሚታደገን ወደተፈጥሮ መመለስ ነው። ወደአረንጓዴነት። እርሱም ፈጣሪ ያበጀው የተፈጥሮ ደምግባት ነው።
ወደተፈጥሮ እስካልተመለስን ድረስ ሞታችንን መግደል አንችልም። ወደአረንጓዴ አስተሳሰብ እስካልመጣን ድረስ አረንጓዴ ምድር መፍጠር አይቻለንም። ምድር አሁን ላይ የተፈጥሮ ቀሚሷን አውልቃ ርቃኗን ናት። ሁላችንም ሀፍረተ ስጋዋ ፊት ቆመን የምናላግጥ ነን። ምድር ወደተፈጥሮዋ እስካልተመለሰች ድረስ መኖራችን ጥያቄ ውስጥ የሚወድቅ ነው።
ይሄን አይነቱን የተፈጥሮ ሚዛን ለመጠበቅና ለማስተካከል በመንግሥት በኩል ቁርጠኛ አቋም እየተወሰደ ይገኛል። ያለፉት አራት ዓመታት እንደ ዓለም የተጋረጠብንን የህልውና ስጋት ለመመከት ችግኝ በመትከል ሃላፊነታችንን ስንወጣ መቆየታችን ይታወሳል። በዘንድሮው የክረምት ወቅትም እንዳለፈው ጊዜ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ /ዶክተር/ መሪነት በህዝቡ ተሳትፎ በርካታ ችግኞችን በመትከል የአየር ንብረት ለውጥን ለመጠበቅ እንቅስቃሴ ጀምረናል። ‹ነገን ዛሬ እንትከል› በሚል መሪ ቃል።
ያለፉትን ጊዜአቶች ማስታወስ ብንችል በአረንጓዴ ዐሻራ ፕሮግራም ከአፍሪካ አልፈን በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ያገኘንበት ተሳትፎ ነበር። የጉዳዩ አሳሳቢነት ምን ያክል እንደሆነ የተረዳው መንግሥት በአራት ዓመቱ የልማት እቅድ ውስጥ እንደ አጀንዳ ይዞ የትግበራ ሂደቱን ከፊት ሆኖ ሲመራው ቆይቷል። አፍሪካ በብዙ ችግሮች የምትናጥ አህጉር ነች ። ድህነት፣ ሃላቀርነት በዚህ ላይ ደግሞ አሁን አሁን የአካባቢ የአየር ለውጥ ዋነኛ ገፈት ቀማሽ ነች። በድህነት ተቆራምዳ ለሰው ሰራሽ ችግሮች ሰለባ ለሆነችው አፍሪካ በአረንጓዴ ዐሻራ ፕሮግራም ላይ ንቁ ተሳትፎ ማድግ ሚኖረው አስተዋጽኦ ከፍያለ ነው።
በአየር ለውጥ ሳቢያ የሚመጡ ስጋቶች የመላው ዓለም ስጋት ቢሆኑም በዋናነት ግን አፍሪካን የሚያጠቁ ናቸው። የበለጸጉት ሀገራት የችግር ምንጭ የመሆናቸውን ያክል ችግሩን የሚቋቋሙበት ዘዴና መላ ከወደ ቴክኖሎጂያቸው በኩል አላቸው። የእኛ የአፍሪካውያን ብቸኛ መዳኛችን የአረንጓዴ ልማት ዐሻራን እውን ማድረግ ነው። አፍሪካ በተለይም የአፍሪካ ቀንድ ሀገራት በድርቅ ሳቢያ ዜጎቻቸውን ለርሃብና ለሞት ሲዳርጉ ዓመታትን አስቆጥረዋል። “በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ” እንደሚባለው ከአንዱ በሽታችን ሳናገግም በሌላ በሽታ መጠቃታችን የአፍሪካ መገለጫ ሆኖ ለዘመናት ሰንብቷል።
ስጋቱን ከፍ ያደረገው ደግሞ በየአስር ዓመቱ ቤታችንን አንኳኩቶ ይመጣ የነበረው ድርቅና ርሀብ በየዓመቱ መምጣቱ ነው። ይሄ መሰሉ ያልተለመደ ለውጥ እንዴት መጣ ብለን ስንጠይቅ የምናገኘው አንድ መልስ ነው እርሱን የአየር ንብረት መዛባት የፈጠረው ነው የሚል ነው። በየዓመቱ አይደለም በየአስር ዓመቱ እንኳን ድርቅና ርሃብ ያማል። አባቶች ከርሃብ ጦርነት ይሻላል ይላሉ። ጦርነትም ርሃብም አይሻለንም። ግን ሁለቱን ሚዛን ላይ ብናስቀምጣቸው አንዱ ሻል ብሎ የምናገኘው ይመስላል። ከሁለት መጥፎ አንድ መጥፎ ማለት ነው። እንግዲህ ቀጣናችን የአፍሪካ ቀንድ እንዲህ ባለው ከጦርነት በላይ በከፋ ርሃብ የምትሰቃይ ናት።
ድርቅና ርሃብ መጥቶብን አይደለም ወትሮም በቀን ሶስት ጊዜ መብላት የሚያንገዳግደን ህዝቦች ነን። የቀጣናው ስጋት ከእንዲህ አይነቱ የህልውና ስጋት የሚተርፍበት አንድ መንገድ አለው.. የአረንጓዴ ዐሻራ ንቅናቄ። የአረንጓዴ ዐሻራ ንቅናቄ በየዓመቱ የሰኔን መግባት ተከትሎ የሚተገበር ብሄራዊ ንቅናቄ ነው። አፍሪካ በተለይም በጦርነትና በሌላም ችግሮች የሚሰቃየው የአፍሪካ ቀንድ በአስር ዓመት አንድ ጊዜ የሚጎበኘው ድርቅና ርሃብ በየዓመቱ መከሰቱ አደጋው ምን ያክል እንደሆነ መገመት አይከብድም። እንዲህ አይነቱ አደጋ ዓመት በዓመት እየመነመነና እየሳሳ ከመጣው የአካባቢ ጥበቃ እሳቤ ማነስ መሆኑ የማይታበል ቢሆንም መፍትሄ ተኮር እንቅስቃሴ እንደሚያሻ አመላካች ነው።
ፍሪካ በአየር ንብረት ለውጥ ያልታመመችበት ጊዜ ባይኖርም እንደ ፈረንጆቹ ከ1970 ወዲህ ግን ህመሟ ወደጣር ተቀይሮ እዬዬ በማለት ላይ ናት። በተለይ ምስራቅ አፍሪካ በዚህ የአየር መዛባት ብዙ ነገሯን እያጣች ያለችበት ሁኔታ እንዳለ ብዙ አመላካች እውነታዎች አሉ። ህመሟን የከፋ የሚያደርገው ደግሞ በግራና በቀኝዋ ታካ የያዘችው የሰሀራ በርሃና ሳይጎበኛት የማያልፈው የድርቅ ወቅት ነው። ወትሮም ድህነት መገለጫዋ የሆነው እና በእርዳታ ህልውናዋ የቆመው ምስራቅ አፍሪካ ከየትኛውም ሀገርና ህዝብ በላይ የህልውና አደጋ ተጋርጦባታል።
እንደመንግሥት የአረንጓዴ ልማት እሳቤ እንዲህ አይነቱን ከአፍሪካ ቀንድ አልፎ አፍሪካን የሚበጅ ከፍ ሲልም ለዓለም የአየር ንብረት ስጋት መልስ የሚሰጥ እንቅስቃሴ መሆኑ ታምኖበት ትግበራ መጀመሩ ‹ቀድሞ መንቃት› ‹ሳይቃጠል በቅጠል› የሚል አቻ ትርጉም ከመስጠት ባለፈ ይበል የሚያሰኝ ቁርጠኝነት ነው። ይሄን አይነቱን ሁለንተናዊ ቀውስ ለማስቀረት በመንግሥት በኩል እየተወሰደ ያለው የቁርጠኝነት ግስጋሴ ምስራቅ አፍሪካን ከስጋት እንደሚታደጋት እሙን ነው። በቀጣይ የሚተከሉት ችግኞችና የተተከሉት ችግኞች ወደዛፍነት ተቀይረው በአየር ንብረት ለውጥ ላይ ሚዛን ደፍተው የሚፈለገው ውጤት ሲመጣ ውሳኔአችን ምን ያክል ትክክል እንደነበር እንረዳለን።
መንግሥት ለጉዳዩ ትኩረት መስጠቱን የሚያመላክቱ በርካታ እውነቶች ከፈረንጆቹ 2019 ጀምሮ መታየት ጀምረዋል። በአረንጓዴ ዐሻራ በኩል የመንግሥት ቁርጠኝነት የት ድረስ እንደሆነ በተወካዮች ምክርቤት በኩል በተደረገ ጥናት በመንግሥት እየተመራ ያለው የአረንጓዴ ልማት እምርታ ማሳየቱ አንዱ ተጠቃሽ ነው።
በመጀመሪያው የአረንጓዴ ዐሻራ ንቅናቄ ከተተከሉት ችግኞች ከ83 ከመቶ በላይ የጸደቁ ሲሆን በቀጣዩ የክረምት ወር ከተተከሉት ውስጥ ደግሞ 80 ከመቶ የሚሆኑት መጽደቃቸውን የመንግሥትን ጨምሮ በገለልተኛ አካላት የተደረገ ጥናት አሳውቋል። ይሄ ብቻ አይደለም ችግኞቹ አድገው የሚፈለገውን አገልግሎት በመስጠት የታሰበውን ዓላማ ማስገኘታቸው በጥናቱ ተጠቅሷል። ዛሬ ላይ እያደረግን ያለንው አረንጓዴ ልማት የነገ የመኖር ዋስትናችንን ከማረጋገጡም በላይ ከአየር ንብረት ጋር ተያይዘው ለሚመጡ ችግሮች አስቀድሞ ምላሽ መስጠትም ነው። ከእኛ አርቀን ለሌሎች፣ ከሌሎች ገፍተን ለሚመጣው ትውልድ ስንቅ ማስቀመጥ ማለት እንዲህ ነው።
ከዚህ ራቅ ካለ ደግሞ እንደፈረንጆቹ አቆጣጠር ሁለት አስርት ዓመታትን ሊደፍን ጥቂት በቀረው አፍሪካ ተኮር የልማት ጥንስስ ወይም ደግሞ የአፍሪካ ህብረት የአረንጓዴ ልማት እሳቤን የሚደግፍ፣ የሚመራ፣ የሚያነቃቃ ህዝባዊ ተሳትፎም ጭምር እንደሆነ መናገር ይቻላል። የኢትዮጵያ መንግሥትና የኢትዮጵያ ህዝብ እያደረጉ ያሉት የአረንጓዴ ልማት ትግበራ ከአገር አልፎ አፍሪካን ከአፍሪካም ዓለም አቀፍ እውቅና የተቸረው እንደሆነ በተለያዩ ጊዜ ብዙ የውዳሴና የሙገሳ ድምጾችን ሰምተናል። ለዚህ ምስክር ከሚሆኑን አካላት ውስጥ አንዱ የአፍሪካ ህብረት ነው።
የአፍሪካ ህብረት እስከመጪው 2030 ድረስ የሚተገበር የአረንጓዴ ልማት ፕሮግራም አለው። በአፍሪካ ህብረት በኩል የተያዘው ይህ የአረንጓዴ ልማት ትግበራ በሚፈለገው ፍጥነት፣ በተፈለገው ጊዜ አለመከናወኑ እንደአንድ ጉድለት የሚጠቀስ ሲሆን በተቃራኒው በቁርጠኝነት ከእቅዳችን በላይ በአረንጓዴ ልማት ላይ አሻራችንን እያሳረፍን ያለነው እኛ ለአፍሪካ ህብረት የዝግታ ጉዞ ሃይል እንደሚጨምርለት የታመነ ሆኗል።
የመንግሥት የአረንጓዴ ልማት ፕሮግራም ችግኝ በመትከል የሚያበቃ አይደለም። ለብዙዎች የሥራ እድል ከመፍጠር ባለፈ ማህበረሰቡ ከጓሮው አልምቶ ከጓሮው የሚበላበትን የከተማ ግብርና የመፍጠር ዓላማ ያለው ነው። እራስን በምግብ እህል ለመቻል ለሚደረገውም ጥረት ጥልቅ አቅም የሚሆን ነው። በዘንድሮው መርሀ ግብር ደግሞ ከችግኝ ተከላ ጎን ለጎን በአጭር ጊዜ ውስጥ ፍሬ የሚሰጡ እንደ አቡካዶና አፕል የመሳሰሉ ፍራፍሬዎች በሰፊው ተደራሽ የሚሆኑበት አሰራር ቅድሚያ ተሰጥቶት እየተሰራ እንደሆነ ለማድመጥ ችለናል።
ከጓራችን እየበላን፣ በአረንጓዴ እሳቤ በአረንጓዴ ምድር ላይ ሳይሞቀንና ሳይበርደን፣ በተስተካከለና ስጋት በሌለው ከባቢ ውስጥ ሕይወትን መምራት ከምንም በላይ ደስ የሚል ነገር ነው። ሂደቱ ጊዜ የሚወስድ ቢሆንም ያለፉትን ሶስትና አራት ዓመታት ውጤት እያየን ነው። በቀጣይ ከአፍሪካ ተሻግሮ በዓለም አቀፍ ደረጃ ስማችንን የሚያስጠራ የአረንጓዴ አስተሳሰብ ርዮት እንደምንፈጥር ይታመናል። በበጎ ሃሳብ በጎ ትውልድ መፍጠር አሁን ላይ ላሉብን ለማናቸውም ሀገራዊ ችግሮች መፍትሄ ነው።
‹ነገ ዛሬ መትከል› በእንዲህ አይነቱ ከዛሬ ወደነገ በሚሻገር እና ለትውልድ በሚተርፍ ሃሳብና ተግባር የሚገለጽ ነው። ዛሬ ላይ በየትኛውም ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የምናደርጋቸው ንቃቶች ነጋችንን በተስፋና በትንሳኤ እንድናይ የሚያደርጉ ናቸው። በሚያልፍ እድሜ የማያልፍ ዘመን ተሻጋሪ ጀብድ ሰርተን እንለፍ።
በትረ ሙሴ (መልከ ኢትዮጵ)
አዲስ ዘመን ሰኞ ሰኔ 26 ቀን 2015 ዓ.ም