በተናጠል የቆመ ሰውም ሀገር እንደሌለ ብዙዎቻችን እንስማማለን። ተያይዘንና ተደጋግፈን ከትናንት ዛሬን አይተናል እንጂ ብቻችንን የፈጠርናት ሀገር የለችም። ይህ እውነት ግን ዛሬ ዛሬ የተሸረሸረ ይመስላል። እኔ ባልኖር ኖሮ ይህ ሊሆን አይችልም የሚሉ አካላት ተበራክተዋል። ግለኝነቱ ሰፍቶ ድሃው ከሀብታሙ ተለያይቷል። ቤተሰቡን ቀርቶ ራሱን መመገብ ያቃተው ሰው በየሰፈሩ ተንሰራፍቷል።
wig shop
wig stores
cheap wigs for sale
cheap wigs
cheap lace front wigs
best human hair wigs
real hair wig
cheap human hair wigs
best wigs for white women
wig stores
best wigs on amazon
cheap wigs
short blonde wig
black women wigs
cheap lace front wigs
wig outlet
cheap wigs
black hair wig
best human hair wigs
online wig store
best human hair wigs online
cheap wigs for sale
lace front wigs
cheap wig
cheap wigs
best human hair wigs online
womens real hair wigs
wigs sale
wig types
wig sale
best wigs for black women
human hair lace front wigs
wholesale wigs
wig shop
headband wig
wig sales
human hair wigs for women
wigs sale
wig shops
luvme glueless wigs
wigs online
በዚያው ልክ ደግሞ ‹‹ለምን ኬክ አትበሉም›› አይነት ተግባራት ይታያል። እኛ ኢትዮጵያውያን ችግረኛ ስናይ አብረን የምንቸገር፤ ከህመምተኛው ጋር አብረን የምንታመም ነበርን። ብቻ የሚሉት ነገር በምንም ተአምር አናውቅም። ተጠራርቶ መብላት፣ መጠጣትና ኀዘንን ሳይቀር አብሮ ማሳለፍ ነበር የምናውቀው። ዛሬ ግን የእኔ ቤት እስካልተነካ ድረስ ምን ቸገረኝነቱ ተንሰራፍቷል።
ኢትዮጵያ ትናንትን ያለፈችው በትናንቶቹ አባቶች መደጋገፍና ብርታት እንደሆነ ዘንግተነዋል። ብዙ እጆች የማትደፈር፣ በማንነቷ የምትኮራ እንዳደረጓትም ረስተነዋል። የዛሬዎቹ ትውልዶች ደረታቸውን ነፍተው እንዲጓዙ ማን እንዳደረጋቸው መስማትም አይፈልጉም። ውበቷ፣ ድምቀቷ የትናንትናዎቹ መልካም እሴቶች መሆናቸውን ትተው የውጭ አምላኪዎች ከሆኑ ሰነባብተዋል።
ለመሆኑ ግለኝነት ያሳድረን ይሆን ካልን ፣ መልሱን ሁላችንም እናውቀዋለን። ብቻችንን ይዞን ይነጉዳል እንጂ ምንም አንለወጥበትም። እና ምን ይሁን ከተባለ መልሱ ቀላል ነው። ትናንትናችንን እናስብ፤ ባህልና ወጋችንን እናክብር። መተባበራችን ኃይላችን እንደሆነ እንመን። በአንድነታችን ራሳችንን ብሎም ቤተሰባችንና ሀገራችንን እንደምንገነባ ፤ እንደምንለውጥ እንቀበል። ለተግባራዊነቱም አንመከኛኝ።
ትናንት አንድ በመሆናችን ያመጣናቸው ድሎች ብዙ ናቸው። አንዱ ለጠላት የማንበገር መሆናችን ነው። ችግር የማይንደን እንደሆንም ያሳየን ሕዝቦች መሆናችንን ያስመሰከርነው በህብረት በሰራናቸው ተግባራት ነው። አንተ የንትና ዘር ነህ ከአንተ ጋር አልሆንም ሳይሆን አንተ ኃይሌ ነህ በማለታችን ሀገር ወዳድ ዜጎችን እንድናበረክት አግዞናል፤ እንድንሆን አድርጎናል። በዓድዋ ልዩነቶች ቢኖሩም በአንድነት ሆ ብሎ የመነሳታችን ምስጢርም ይህ ነበር።
ይህ ባህላችን ‹‹ ከአንድ ብርቱ ሁለት መድሃኒቱ፤ 50 ሎሚ ለአንድ ሰው ሸክሙ ለብዙ ሰው ጌጡ፤ ድር ቢያብር አንበሳ ያስር›› ወዘተ እየተባባልን አንድነት ኃይል፣ ብርታትና አቅም እንዲሆንም አስችለነዋል። ዛሬም ማስቀጠል ያለብን ይህንን ነው። በእነዚህ እሴቶች ደስታና ኀዘናችን እኛን ገንብቶን ያልፋል። እኛ የእኛ ብቻ ሳንሆን የሁሉም እንደሆንን ያስረዳናል። በጋራ እየኖርን ዛሬን፣ ነገን አይተን ከነገወዲያን ለልጆቻችን እናተርፋለን።
ኢትዮጵያ ለአንድ ወገን የምንተዋት አይደለችም። መንግሥት ብቻውን ምንም አያደርጋትም። አንድ ሰው ወይም ኃላፊነት የተሰጠው አካልም ብቻውን ምንም ሊፈይድላት አይችልም። እኛ እኛ ስንሆን ነው በአብሮነታችን የምንሻትን ሀገር ልንገነባ የምንችለው። በመነጋገር፣ በመተሳሰብ ለሰዎች ሁልጊዜ በጎውን በማሰብ መጓዝ ይገባናል። በተለይ አሁን ሀገራችን ባለችበት ሁኔታ ብዙ ሰዎች በጎነትን ይሻሉ፤ የሚያረጋጋቸው፣ ከእርዛትና ከርሃብ የሚታደጋቸውን ይፈልጋሉ። ያ ሰው ደግሞ እኛ መሆን አለብን።
ህብረትና አንድነት የፈጠሩት ኢትጵያዊነት መቼም ቢሆን አይደበዝዝም፤ ህብረታችን በበጎነታችን ይገለጥ። መጪው ደግሞ ክረምት በመሆኑ ብዙ የምንሰራቸው በጎ ተግባራት ከፊታችን ይጠብቁናል። ክረምት ለቅዝቃዜው ኩታ ይፈልጋል። ይህ ኩታ ደግሞ ብዙ መልክ አለው። አንድም አልባሳቱ ሲሆን የታረዙትን የምናለብስበት ይሆንልናል።
በሌላ በኩል ኩታ በየመንገድ ዳር የወዳደቁትን አንስተን ከሞቀ ስፍራ ላይ የምናስቀምጥበት ጊዜ እንደሆነ ይነግረናል። ሻገር ስንል ደግሞ ኩታ ጣሪያና ግርግዳም ይሆናል። ብዙ የወላለቁ ቤቶች በየአካባቢያችን አይጠፉምና እነርሱን ጠጋግነን ክረምቱን በደስታ የሚያሳልፉና የሚመርቁን አባቶች፣ እናቶችን እንፈጥርበታለን። በዚህች ምድር ከሀገር በላይ ትልቅ ነገር የለንም።
ሀገር የተሰራችው ደግሞ በእነዚህ እናቶችና አባቶች ነው። እናም እነርሱን የምናስታውስበት ጊዜ ስለሆነ እነጠቀምበት። ለዚህ ደግሞ እንደመንግሥት እድሎች ተመቻችተውልናል። አንዱ የክረምት ወራት የወጣቶች የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ማስጀመሪያ መረሐግብር ነው። የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ከአጋር አካላት ጋር በመተባበር የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ማስጀመሪያ መርሐግብር “በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ” በሚል መሪ ሃሳብ ጀምሮታል።
በመክፈቻ መረሐ ግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት የሴቶችና ማሕበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ እንደተናገሩት፤ በ2015 ዓ.ም የክረምት ወራት የወጣቶች የበጎ ፈቃድ አገልግሎት እና የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐግብር ከ20 ሚሊዮን በላይ ወጣቶች ይሳተፉበታል። በመርሐግብሩ ከ 51 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ ያደርጋል።
የበጎ ፈቃድ አገልግሎቱ የማዕድ ማጋራት፣ የአደጋ ቅድመ መከላከል፣ የአረንጓዴ ዐሻራ፣ የትውልድ ግንባታ፣ የጤናና ቀይ መስቀል፣ የፀረ ኤድስ ዘመቻ፣ የመንገድ ትራፊክ አገልግሎት፣ የሰላም እሴት ግንባታ፣ የኪነጥበብና መዝናኛ፣ የሙያ በጎ ፈቃድ አገልግሎቶች፣ የደም ልገሳ፣ የአቅመ ደካማ ቤቶች እድሳት እና ሌሎችን ያላከተተ ነው ። አገልግሎቱም ከ15 ቢሊዮን ብር በላይ ውጪ ሊሆንበት እንደሚችልም ተገምቷል። ይህ ደግሞ የሰውን ጉልበት ጭምር ታሳቢ አድርጎ ነው። ስለሆነም እኛ ማህበራዊ መስተጋብራችንን አጠናክረን የአገልግሎቱ አካል መሆን ይጠበቅብናል።
በዚህ ሥራ መሳተፍ ራስን መታደግ ነው። ምክያቱም ኢትዮጵያ ከሌለች ማንነታችን ይጠፋል። የመኖራችን ምስጢር ያከትምለታል። ታሪካችን በጥልቅ ጉድጓድ ውስጥ ይቀበራል። እናም ሀገር የመጠበቅ ኃላፊነት የእያንዳንዳችን ነውና ለራሳችን ስንል ከችግሮቿ እንታደጋት። በተለይም ማህበራዊ መስተጋብራችን መጠናከር ላይ ያላሰለሰ ጥረት ማድረግ አለብን። እርሱን የሚሸረሽሩትን ማንኛውንም ነገር ልንጋፈጠው ይገባል። እስካሁን ድረስ ኢትዮጵያን ያደመቀው ማህበራዊ እሴቶቻችን በመኖራቸው ነው። ኢትዮጵያ የተጠቀመችውም ውህደታችን በማህበራዊ መስተጋብራችን ውስጥ ስለሚታይ ነው።
ማህበራዊ እሴቶቻችን በአንተ ትብስ አንቺ ትብስ የጠነከሩ ናቸው። እናም ጸባችን ከሮ ውድቀታችን እንዳይፋጠን አድርገውናል። ህዝብ እንዲቀድም፣ ትውልድ እንዲጸና ሰው ለሰው እንዲኖርም መሠረት ሆነውናል። በጨለማው ውስጥ ደማቅ ብርሃንን እያሳየን በተስፋ እንድንመላለስም አድርገውናል። በተለይም ዋነኛ መገለጫው በሆነው በጎነት አማካኝነት ሰው ቂሙን ጭምር ይረሳል። ነገሮችን አብሮ ማሳለፍ፤ መተጋገዝና ለችግሮች እጅ አለመስጠት፤ ግላዊ አስተሳሰብን አስወግዶ ማህበራዊነትን ማስፋት ለዛሬ ግድ ከሚያስፈልጉን መሠረታዊ ፍላጎቶች ውስጥ ናቸውና እነርሱን በልባችን እናኑራቸው።
ከሀገር ግለኝነትን ስናስበልጥ፣ ከአንድነት መለያየትን ስናስቀድም ኢትዮጵያዊነትን እንሸረሽረዋለን። ስንፎካከር፣ በራስ ወዳድነት ስንቆም ሌሎች በመሀከላችን ገብተው የማንፈልገውን ሥራ ያሰሩናል። እናም እንዳንበተንና እንዳንለያይ በሰላምና በእርቅ ባህላችን እንኑር። ይህ ማንነት ደግሞ ሀገርን ያጸና ብቻ ሳይሆን አፍሪካን ብሎም ዓለምን ያቆመ ነውና በጎነታችንን እናብዛ አበቃሁ ። ሰላም!!
ክብረመንግስት
ይህ አምድ በተለያዩ ፖለቲካዊ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጉዳዮች ዙሪያ ዜጎች ነፃ ሀሳባቸውን የሚሰጡበት ነው።በዓምዱ ላይ የሚወጡ ጽሁፎች የዝግጅት ክፍሉን አቋም አያመለክቱም።
አዲስ ዘመን ሰኞ ሰኔ 26 ቀን 2015 ዓ.ም