የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ሰሞኑን ከመላ አገሪቱ ከተውጣጡ የሕክምና ባለሙያዎች ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል፡፡ በውይይቱም ባለሙያዎቹ ጥያቄዎችን ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ሰንዝረ ዋል፡፡ አብዛኞቹም ጥያቄዎች ትኩረት አልተሰጠንም፣ ጉዳያችን ተዘንግቷል በሚሉት ዙሪያ የሚያጠነጥኑ ናቸው፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከባለሙያዎቹ ጋር ያደረጉት ውይይት ብዙ ትምህርት የተገኘበትና በጣም ጠቃሚ መሆኑን በተለይ ለፖሊሲ አውጪዎች ጠቀሚታ እንዳለው ተናግ ረዋል፡፡ ህግ ለማውጣት ሲፈለግ ሙያተኛውን መሰረት አድርጎ ለማውጣትም መነሻ መሆኑን ጠቅሰው፣ የመረጃ ክፍተትን እንዳለም እንደሚያሳይ አስታውቀዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ውይይቱን እንደ መልካም ጅምር ወስደውታል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐብይ ፣ ከህክምና ባለሙያዎች ለተነሱት ጥያቄዎች በዝርዝር ምላሽ ከመስጠታቸው በፊት መልሱ የሚጀምረው ከአጠቃላይ የአገሪቱ ሁኔታ እንደሆነ ጠቅሰው፤ አጠቃላይ የአገሪቱን ነባራዊ ሁኔታ ማየት ካልተቻለ የዘርፉን ችግር መፍታት እንደማይቻልም አስረድተዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከምንም በላይ የህክምና ባለሙያዎቹ ሲመረቁ ህዝብን በቅንነት ማገልገልንና የህክምና ስርዓቱን ማዘመን እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል፡፡ የህክምና ባለሙያዎቹ ዋናው ተግባርም ሰው መርዳት መሆኑን ጠቅሰው፣ ህይወት ላዳነ ሰው ደግሞ ክፍያው ምን ሊሆን ይችላል በማለትም መልሰው ባለሙያተኞቹን ጠይቀዋል፡፡ ለባለሙያዎቹ ውለታ የሚከፈለው በገንዘብ አለመሆኑንም አክለው ተናግረዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከህክምና ባለሙያዎቹ ጋር ያደረጉትን ቆይታ እንደሚከተለው አቅርበነዋልና መልካም ንባብ ይሁንልዎ፡፡
ጥያቄ፡– መንግስት ለጤናው ዘርፍ በጀት ምደባ የሰጠው ትኩረት አነስተኛ ነው፤ ለምድን ነው ለዘርፉ ትኩረት የተነፈገው?
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ፡- በዚህ ዓመት ብቻ የጤና ሚኒስትሩ አምስት ጊዜ የበጀት ጉዳይ አቅርቧል፡፡ ለምሳሌ ለማንሳት ያህል የማህበረሰብ ፋርማሲ ችግር አለ ተብሎ 50 የጋራ መኖሪያ ቤት እንግዛ ተብሎ በጀት ፈቅደናል፡፡ ባለፈው ዓመት ለጤናው ዘርፍ 30 ሚሊዮን ዶላር ብቻ ነበር የተፈቀ ደው፡፡
በውጭ ምንዛሬ እጥረት ምክንያት ህክምና ተስተ ጓጉሏል ተብሎ ዘንድሮ ሌሎች ችግሮች እንዳሉ ሆነው የተፈቀደው 130 ሚሊዮን ዶላር ነው፡፡ ይህ ማለት በዚህ ዓመት የከፈልነው እዳ 600 ሚሊዮን ዶላር ገደማ ነው፡፡ ይህ የዘንድሮ ብቻ አይደለም፤አምናም አቻምናም እዳው ሳይከፈል በመቆየቱ የተከፈለ ነው፡፡ ስለሆነም እዳውን በተወሰነ መልኩ ማስተንፈስ ካልቻልን ብዙ ችግር ይኖራል፡፡ ለዘርፉ ትኩረት ባይሰጥ ኖሮ እዳ መክፈል እያለብን አምና 30 ሚሊዮን የነበረውን 40 ወደ 50 እንዲደረግ ስንል ችግር ለማቃለል ብለን የሰጠነው 120 ሚሊዮን ዶላር ነው፡፡
ጥያቄ፡– አገሪቱ ላይ ያለው የመድኃኒት አቅርቦት ችግር ተሻሽሏል ተብሎ በተደጋ
ጋሚ ይነገራል፡፡ ይሁንና አሁንም ቢሆን በጣም ከፍተኛ ችግር ነው ያለውና ይህንን ችግር ለመፍታት በመንግስት በኩል ምን አይነት መፍትሄ እየተፈለገለት ነው ?
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ፡– ከመድ ኃኒት አንፃር ዘንድሮ ብቻ ስድስት ፋርማሱቲካል ኩባንያዎች ወደ እኛ ኢንዱስትሪያል ፓርክ ገብተዋል፡፡ ይህም በጣም የመንግስት ከፍተኛ የትኩረት አቅጣጫ ነው ተብሎ ባሀብቶች በመጠየቃቸውና እንደ ቅድመ ሁኔታ የሚያ ነሷቸው ጉዳዮች በእኛ በኩል ለማሟላት ጥረት ስላደረግን ስድስት ፋብሪካዎች ስራ ጀምረ ዋል፡፡ ይህ የትኩረቱ አንድ አካል ተደርጎ ቢወ ሰድ መልካም ነው፡፡
ጥያቄ ፡– በጤና ጣቢያ ለሚሰሩ ባለሙያዎች የሚሰጠው ትኩረት አነሰተኛ እየሆነ መጥቷል፤ የቤት አቅርቦቱም ቢሆን የሚፈለገውን ያህል መንግስት ትኩረት አልሰጠውምና እዚህ ላይ ምን ታስቧል ?
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ፡– ዘንድሮ በ354 ጤና ጣቢያዎች ላይ 4 ሺ 248 ቤቶች ተሰርተዋል፡፡ እናም ዘርፉ ምንም ነገር አላገኘም ካላችሁ ሌላው ደጋሚ ምን ይላል የሚል ጥያቄ ያስነሳብኛል፡፡ ነገር ግን ዘርፉ ከዚህ በላይ ያስፈልገዋል ወይ ቢባል ምንም ጥያቄ የለውም፤ያስፈልገዋል፡፡ ከዚህ በላይ ጤና ዘርፍ ላይ ኢንቨስት ካላደረግን ሰው
ብናስተምርም፣ ብንወልድም ጤና ከሌለ አገርም ጤና አይኖረውም፡፡ በመሆኑም ዘርፉ ላይ ትኩረት ሰጥቶ መስራት ያስፈልጋል፡፡ ነገር ግን የተደረገውን በሙሉ ምንም እንዳልተደረገ ካደረጋችሁ ስህተት ይሆናል፡፡
ጥያቄ ፡– የጤና ባለሙያው ከሚያገኘው ዲውቲ እንደ ደቡብ ክልል ታክስ ይቆረ ጣልና ይህ አግባብ ባለመሆኑ እዚህ ላይ ምን የታሰበ ነገር አለ?
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ፡- ዲውቱ ላይ ታክስ የሚጫንባቸው አካባቢዎች ሁሉም አይደሉም፡፡ ነጻ የተደረጉ አሉ፡፡ ለዚህም መንግስት በአንድ ወር 70 ሚሊዮን ብር ያጣል፡፡ ይህን ጉዳይ ጠይቃችኋል? ደግ ሞም ከዲውቲ ታክስ መክፈል የለባችሁም በሚል ተወስኗል፡፡ ጉዳዩ የተወሰነውም በፌዴራል ደረጃ ነው፡፡
ይሁንና በሁሉም አካባቢ እኩል አይነት አሰራር አልያዘም የሚለውን በተመለከተ በአሁኑ ወቅት በውይይቱ ላይ የሁሉም ክልሎች ጤና ቢሮ ኃላፊዎች ስላላችሁ በየክልላችሁ አብዛኛው ሙያተኛ ያነሳውን ሐሳብ ወስዳችሁ ከክልል ርዕሰ መስተዳድሮች ጋር ተጨማሪ ውይይት ማድረግ አለባችሁ፡፡ የክልል ፕሬዝዳንቶችም አማራ ያለው ከትግራይ፣ ትግራይ ያለው ከኦሮሚያ ስለሚለያይ አንዳንዱ ዘንድ ጉዳይ የሆነው ሌላው ክልል ላይሆን ይችላልና ተጨ ማሪ ዝርዝር ያለ ውይይት ማድረግ ይኖር ባችኋል፡፡
ጥያቄ፡– ከደመወዝ ጭማሪ ጋር በተያያዘ መንግስት ምን አስቧል?
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ፡– ደመወዝን በሚመለከት ጥናቱን እናይና ብንጨ ምር ብንጨምር ዘጠኝ ሺ ለሚበላው ሰራተኛ እስከ 500 ብር ብቻ ስለሚሆን ይህ ትርጉም አይኖረውም፡፡ እንዲያውም በአሁኑ ወቅት ደመወዝ ስለመጨመር ብንነጋገር የዘይትና የሌላውን ሸቀጥ ዋጋ እንዲጨምር መንገድ ከመክፈት ባሻገር ምንም ዋጋ የለውም። ምክን ያቱም መንግስት ምን ያህል ማድረግ እንደሚችል ያው እናንተው የምታውቁት ነውና ነው፡፡
ጥያቄ፡– የኮስት ሼሪንግ (የወጪ መጋራትን) በተመለከተ የሚደርስብን ተጨ ማሪ ክፍያ ዲግሪያችንን ለመቀበል እንኳ እንቅፋት ሆኖብናልና እዚህ ላይ መንግስት የሚሰጠው መፈትሄ ምንድን ነው?
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ፡– እንደማ ንኛውም ሙያ ኮስት ሼር ማድረግ (ወጪን መጋራት) አለባችሁ፤ ይህ ለድርድር የሚቀርብ ጉዳይ አይደለም፡፡ ምክንያቱም የምታውቁት ነው፡፡ ነገር ግን ህክምናን በሚመለከት ገንዘብ ከሚፈለግ አንድ ሰው ከተመረቀ በኋላ በዚያች አነስተኛ ደመወዝ አምስት እና አስር ዓመት ሰርቶ ያካክስ ሊባል ይችላል፡፡ ይህን ጉዳይ ተወያይታችሁ በፖሊሲ ማየት ነው፤ እሱ ብዙ አያስጨንቅም፡፡ በጥሬ ገንዘብ ብቻ ሳይሆን በዚህም መልክ መክፈል ይቻላልና ነው፡፡
ሰራተኛው ከተመረቀ በኋላ ሲያገለግል በአነስተኛ ደመወዝ ስለሚሆን ተጨማሪ ስራ ስለሚጠበቅበት ማለትም አንዳንድ ቦታ አንድ ሙያ ያላቸው ሰዎች ሁለት ሶስት ስራ ስለሚሰሩ አምስት ወይም አስር ዓመት ማገልገል በራሱ እንደ መክፈል ይቆጠር የሚል ነገር ሊታይ ይችላል፡፡ ይህን ጉዳይ በውይይት አይተን ልናዳብረው እንችላለን፡፡ ግን ደግሞ ያላችሁት ተጨማሪ ክፍያው መቆሙን ነው፡፡
አዲስ ዘመን ሚያዝያ 29/2011
በጋዜጣው ሪፖርተር