መርድ ክፍሉ
ወጣት ቢንያም ጥላሁን በምንጃር ሸንኮራ ወረዳ ነዋሪ ነው:: በአካባቢው የሚገኙ ችግረኞችን ሲመለከት እነሱን ለመርዳት ሀሳብ መጣለት:: በአካባቢው የሚገኙ ደጋፊ የሚፈልጉ ሰዎች ለበጎ ስራ እንዳነሳሱት ይናገራል::
በተለያዩ አጋጣሚዎች ሰዎች ከነበሩበት የኑሮ ደረጃ ዝቅ ሊሉ ይችላሉ:: እነሱን ለማንሳትና ለመደገፍ በቴሌግራም ግሩፕ በመፍጠር ስራው ተጀመረ:: በአረብ አገር የሚኖሩ ሰዎች ለማህበሩ መመስረት ከፍተኛ ድጋፍ አድርገዋል::
ማህበሩ ሲመሰረት አላማው ለተቸገሩ ሰዎች የእለት ጉርስ መስጠት ሲሆን ማንኛውም ሰው ድጋፍ ለማድረግ በተከፈተው የባንክ አካውንት ገንዘብ ያስገባል:: ከዛም ገንዘብ ያስገባበትን ደረሰኝ በቴሌግራም ግሩፑ በኩል እንዲለጠፍ ያደርጋል:: በዚህም ማህበሩን ለመርዳት ቃል የገቡ ሰዎች ማስገባት አለማስገባታቸው ይታወቃል:: የኮቪድ 19 ወረርሽኝ ተደራቢ ችግር እንዳይፈጥር ማህበሩ ጠንክሮ እየሰራ የሚገኝ ሲሆን አሁን በማህበር ውስጥ ያለው አባል በቂ ባለመሆኑ ሌሎችንም ለመጨመር ታስቧል::
የበጎ ስራውን ሃሳብ ወጣት ቢንያም ሲመጣ የተደላደለ ነገር ባይኖርም ሀሳቡን ብዙዎች ደግፈውለታል:: ድጋፍ የተደረገላቸውን ሰዎች የደስታ ስሜት ማየት በራሱ የህሊና እረፍትም ሰጥቷቸዋል:: ድጋፍ የሚደረጉ ቁሳቁሶችን ካሰባሰቡ በኋላ ለማን ይሰጥ የሚለው ጉዳይ ከባድ ነበር:: ይህን ሁኔታ የቀበሌ አመራሮች እንዲፈቱት ወደነሱ ተላከ:: ቀበሌውም ችግረኛ ናቸው ያለውን ሰዎች ስም ዝርዝር ለማህበሩ አሳወቀ::
ከተላከው ስም ዝርዝር ውስጥ በባሰ የኢኮኖሚ ችግርና በጉልበታቸው ሰርተው መኖር የማይችሉ ሰዎች ተለዩ:: በተጨማሪም በተቋም ስር የሚገኙ ስምንት አቅመ ደካሞች ወደ ማህበሩ እንዲመጡ ተደርጓል::
በግል ከሚሞከሩ ነገሮች ምንም አይነት ችግር የሚቀርፍ አይደለም:: በጋራ በመሆን ስራዎች ሲሰሩ አንድ እርምጃ መሄድ ይቻላል:: ለዚህ ደግሞ እናት በጎ አድራጎት ማህበር ለምሳሌነት ማንሳት ይቻላል:: በማህበራዊ ሚድያ በኩል ወጣቶች ንቁ ተሳትፎ ያደርጋሉ:: አብዛኛው ወጣት አፍራሽ በሆኑ ተግባራት ላይ ሲሳተፍም ይታያል:: ነገር ግን ማህበራዊ ሚድያዎችን ለበጎ ተግባራት ማዋል ጥቅም እንዳለው ማህበሩን እንደ ምሳሌ ማንሳት ይቻላል:: ማህበራዊ ሚድያዎች ለመጥፎ ሳይሆን ለበጎ ነገሮች የተፈጠሩ ናቸው:: ወጣቱ የትኛውን መንገድ መርጦ መጠቀም እንዳለበት ሊያስተውል ይገባል::
ነገር ግን የመረዳዳትም ሆነ በልክ የመኖር ባህሎች ዛሬም እንዳሉ የሚያሳዩ ተግባራት እንዳልጠፉ በርካታ ማሳያዎችን ማንሳት ይቻላል። በተለይ በቅርቡ የኮቪድ 19 ወረርሽኝ መከሰትን ተከትሎ በርካታ ዜጎች ለከፍተኛ የኑሮ ጫና መዳረጋቸው ይታወሳል። ይህንን ክፉ ጊዜ ለማለፍ ደግሞ የደጋግና ቅን ልቦች መኖር ትልቅ አስተዋፅኦ ማድረጉን ስንመለከት የመረዳዳት ባህላችን ዛሬም ጠንካራ መሆኑን እንገነዘባለን።
ዛሬ በምንጃር ሸንኮራ የሚገኘውና በአካባቢው የሚገኙ አቅመ ደካማ ሰዎች የሚደግፈው እናት በጎ አድራጎት ማህበር እንቃኛለን:: እናት በጎ አድራጎት ማህበር መስራችና ሊቀመንበር ወጣት ቢንያም ጥላሁን ከጓደኞቹ ጋር በመሆን ማህበሩን መስርቷል:: ከወጣት ቢኒያም ጋር ያደረግነውን ቆይታ እንደሚከተው አቅርበነዋል::
አመሰራረቱና የሰራቸው ስራዎች
እናት በጎ አድራጎት ማህበር የተመሰረተው ግንቦት 18 ቀን 2012 ዓ.ም ላይ ነው:: ሲመሰረት ዋና አላማው የነበረው በወቅቱ ተከስቶ የነበረውን የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ በአቅመ ደካማዎች ላይ የሚደርሰውን ችግር ለመቅረፍ ነበር:: የመንግስት ሰራተኛው ያለውን ደመወዝ ይዞ ስሚወጣ ለችግር ብዙ ላይጋለጥ ይችላል::
ነገር ግን አቅም የሌላቸው ሰዎች ችግር ላይ ስለሚወድቁ እነሱን ለማገዝ ገንዘብ እናሰባስብ በሚል በቴሌግም ዘመቻው ተጀመረ:: ሀሳቡ እየተጠናከረ ሲመጣና የሰውም ተሳትፎ ጥሩ ስለነበረ ብዙ ሰዎችን ተደራሽ ማድረግ ተችሏል:: ማህበሩ ከተመሰረተ ጀምሮ ወደ 108 ሺህ 185 ብር አካባቢ ሰብስቦ በቁሰቀቁስ ድጋፍ የተደረገበት ሁኔታ አለ::
ማህበሩ በተለያዩ ዙሮች ድጋፍ ያደረገ ሲሆን የዘይት፣ በርበሬ፣ ሽሮ እና መሰረታዊ ሸቀጦች አቅም ለሌላቸው ሰዎች ተሰጥቷል:: ድጋፍ የሚደረግላቸው ሰዎችን ቀበሌዎች መልምለው የሚያመጡ ሲሆን ለ33 ሰዎች በየዙሩ ድጋፎች ተደርገዋል:: በሻሸመኔ ለተፈናቀሉ ማህበረሰቦች አስራ አራት ሺህ ብር ድጋፍ ተደርጓል:: ህፃናት ከትምህርት ገበታቸው በቁሳቁስ እጥረት እንዳይስተጓጎሉ 31 ደርዘን ደብተር ድጋፍ ተደርጓል::
ማህበሩ በአካባቢው የሚገኙትን ሰዎች ለማገዝ የተቋቋመ ሲሆን በመጀመሪው ዙር በገንዘብ ደረጃ እርዳታ የተደረገው 16 ሺህ 150 ብር ነው:: ይህ የተከናወነው በጥሬ ገንዘብ ሳይሆን በአይነት የተደረገ ድጋፍ ነው:: ምክንያቱም ድጋፍ የሚደረግላቸው አረጋውያን በመሆናቸው በጥሬው ገንዘቡ ቢሰጣቸው ላልተገባ ነገር ሊያውሉት ይችላሉ በሚል ፍራቻ ነው:: ለአረጋውያኑ ዘይት፣ በርበሬና ሌሎች ለምግብ የሚውሉ ሸቀጦች ተገዝተው ተሰጥቷቸዋል::
በሌሎች አካባቢዎች ላይ የሚገኙ ችግረኞችን ለማገዝ ማህበሩ ጥረት እያደረገ ይገኛል:: በሁለተኛው ዙር ለሻሸመኔ ተፈናቃዮች አስራ አራት ሺህ ብር በተከፈተው አካውንት ገቢ ተደርጓል:: በሶስተኛው ዙር 22 ሺህ 185 ብር ወጪ በማድረግ ለገና በዓል ለ56 ሰዎች እንደየፍላጎታቸው ድጋፍ ተደርጓል::
ይህ ማለት ልብስ፣ የምግብ ሸቀጥ ለሚፈልጉ እንዲሁም ለአዕምሮ ህሙማን በቋሚነት እገዛ ለሚደረግላቸው ሶስት ልጆች ምሳ የሚመገቡበት ሁኔታ መፍጠር ተችሏል::
በአራተኛው ዙር በተመሳሳይ 21 ሺህ ብር ወጪ በማድረግ የቁሳቁስ ድጋፍ ተደርጓል:: በአምስተኛው ዙር ደግሞ 17 ሺህ 850 ብር ድጋፍ የሚደረግላቸው ሰዎች በገንዘብ የሚያከናውኑት ጉዳይ ይኖራቸዋል በሚል በጥሬ ገንዘብ ለ32 ሰዎች አምስት መቶ ብር ተሰጥቷል:: በሌላ በኩል አንድ ስለት የነበረባት ሴት ለማህበሩ አስር ሺህ ብር በመስጠት ድጋፍ የሚደረግላቸው ሰዎች እንዲጋበዙ ተደርጓል::
የተሰሩ ስራዎች በየጊዜው የሚገመገሙ ሲሆን በዚህም የወረዳው አመራሮች ንቁ ተሳትፎ ያደርጋሉ:: የማህበሩ ገንዘብ ማስቀመጫ አካውንት የተከፈተው ተፅዕኖ በሚፈጥሩ ሰዎች ነው:: ሰዎቹ የተመረጡት ገቢያቸው ከፍ ያለና ለገንዘብ የማይስገበገቡ እንዲሁም በህዝቡ ታማኝነት ያላቸው ሰዎች ናቸው::
በማህበር ውስጥ ያለው አባል ከማስተባበር የዘለለ የገንዘብ ጉዳይ ላይ ጣልቃ አይገባም:: ማንም ሰው ድጋፍ ከሚያደርግ ሰው ገንዘብ መቀበል አይችልም:: እቃዎችም ሲገዙ ገንዘብ ከሚቆጣጠሩት ሰዎች ውጪ ማንም ሰው እቃ መግዛት አይችልም:: ማህበሩን ለማጠናከር ቲሸርቶች ለማሰራት ታስቧል::
የህብረተሰቡ አቀባበል
የበጎ አድራጎት ስራው ሲጀመር የህብረተሰቡ አቀባበል በሁለት ፅንፍ የተወጠረ ነበር:: ሀሳቡ ሲመጣ ጀምሮ የተወሰኑ ሰዎች ከዚህ በፊት የሚደረገውን በማየት ወይም ደግሞ ውስጣቸው ያለውን ፍራቻ በመመልከት ብቻ አይሳካም በሚል ተስፋ ይቆርጣሉ:: የመደገፍ ሀሳቡ ወደ መሬት ወርዶ ተግባር ላይ ሲውል ሁሉም ሰው ተደስቶ ድጋፍ እያደረገ ይገኛል:: በገንዘብ ለማገዝ አቅም ባይኖራቸው በጉልበት እያገዙ ናቸው::
ማህበሩ ገና ከምስረታው ጀምሮ በወረዳው የነበሩ አመራሮች ከማማከር ጀምሮ ማለትም ህጋዊ ማዕቀፍ ማህበሩ እንዲኖረው ለማድረግ እና በምን መልኩ መንቀሳቀስ እንደሚቻል ሰፊ ስራዎች በጋራ ተከናውነው ነበር:: እያንዳንዱ የማህበሩ ስራ ግልፅ በሆነ መንገድ የሚከናወን በመሆኑ እንዲሁም በወረዳው የሚገኙ አመራሮቸ የማህበሩ አባል እንዲሆኑ ተደርገዋል:: በዚህም እያንዳንዱ እንቅሰቃሴ ላይ ተሳትፎ እንዲያደርጉ በር ከፍቷል:: በእያንዳንዱ ፕሮግራም ላይ የወረዳው ኮሙኒኬሽን በስፍራው ይገኛል:: ማህበሩ በተለያዩ ጊዜያት ከአስተዳደሩ የእውቅና ወረቀት አግኝቷል::
ያጋጠሙ ችግሮች
ማንኛውም ስራ ሲሰራ ብዙ ውጣ ውረዶች አሉት:: በቡድን የሚሰራ ስራ ቀርቶ አይደለም በአንድና በሁለት ሰው የሚሰራ ስራ ችግር ያጋጥመዋል:: የመጀመሪያው ችግር የነበረው የግንዛቤ አለመኖር ነበር:: ይህ ሲባል በበጎ አድራት ስራ የተወሰነ ሰው የሚበለፅግበት እንዲሁም ድጋፍ የሚደረግላቸው ሰዎች ቤተሰብ ወይም ሌላ ሰው ይደግፋቸው በሚል የምናገባኝ መንፈሶች ነበሩ::
ሌላኛው ችግር የነበረው ጊዜን እንዴት አድርጎ መጠቀም ይቻላል:: የውይይት ቀን መወሰን ነበር:: አባል የሚደረጉ ሰዎችን ለማብዛት በተሰሩ ስራዎች 612 አባላት በቴሌግራም ግሩፕ ማግኘት ተችሎ ነበር:: ነገር ግን አባል የሆነው ሁሉ በትክክለኛ ስራ ላይ ከመሳተፍ ይልቅ የራሳቸውን ማስታውቂያ የሚለቁበት እንዲሁም ለማይጠቅሙ ጨዋታዎች የሚጠቀሙበት ብዙ ነበሩ:: ስለማህበሩ መጠናከር በሚወራበት ወቅት ግን ተሳትፎ ይቀንሳል::
በስተመጨረሻ በቴሌግራም ግሩፕ ውስጥ ያሉት ሰዎች ቢኖሩም ባኖሩም ንቁ ተሳትፎ እያደረጉ ባለመሆኑ ንቁ ተሳትፎ የሚያደርጉትን መርጦ አዲስ የቴሌግራም ቡድን እንዲከፈት ተደረገ:: በተከፈተው አዲስ የቴሌግራም ግሩፕ የሚከናወኑ ስዎችን ቀድሞ በነበረው ቴሌግራም ግሩፕ የማሳወቅ ስራም ይከናወናል:: ስራዎች ቀድሞ በነበረው የቴሌግራም ግሩፕ በመልቀቅ የአባላትን ቁጥር ለማሳደግ ጥረት ተደርጓል:: በአሁኑ ወቅት ማህበሩ ቋሚ 51 አባላት ያሉት ሲሆን ወርሃዊ መዋጮ ቀጥታ እንዲያዋጡ ምቹ ሁኔታዎች ተፈጥረዋል::
612 ሰው በቴሌግራም ግሩፕ እያለ ጫጫታና ቀልዶች ይበዙበት ነበር:: በአሁኑ ወቅት ግን ቋሚ አባላትን በመለየት ቋሚ የውይይት ፕሮግራሞች በማዘጋጀት ቅዳሜና ማክሰኞ በቴሌግራም ሰፊ ውይይት ይደረጋል:: በወቅቱም ወደ ማህበሩ የገቡ ገንዘቦችን ኦዲት ማድረግ እንዲሁም ሌሎች ነገሮች ይሰራሉ:: የማህበሩ አባላት ገንዘብ በባንክ አስገብተው ደረሰኙን ቴሌግራም ላይ ኦዲት ለሚያደርገው ሰው ይልካሉ::
የማህበሩ ቀጣይ እቅዶች
ድጋፍ ለሚደረግላቸው ሰዎች ቁሳቁስ መስጠትና ምግብ ማብላቱ ብቻ በቂ አይደለም:: በቀጣይ መሰራት ያለበት ነገር ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመነጋገር ለአቅመ ደካሞች በቋሚነት ገንዘብ የሚያገኙበት ለምሳሌ ዶሮ እርባታ ላይ እንዲሰማሩ ጥናት እየተደረገ ይገኛል:: ስራው ምን ያክል አዋጪ እንደሆነና በማን መሰራት እንዳለበት በጥናቱ ይካተታል:: ከስራው ማህበሩ ሊያገኘው የሚችለው ጥቅም በተጨማሪነት በጥናቱ ይዳሰሳል:: ድጋፍ የሚደረግላቸው ሰዎች በቋሚነት እራሳቸውን የሚችሉበት መንገድ ለመፍጠር ታስቧል::
ማህበሩ የገቢ ሁኔታውን በማሳደግ ጨረታዎችን በአባላቱ የማካሄድ ስራ ይሰራል:: ከዚህም ባለፈ ወርሃዊ መዋጮ በማጠናከር ሌሎች የገቢ ምንጮችን በመፍጠር ስራ እየተሰራ ነው:: ማንኛውም በጎ ማድረግ የሚፈልግ ሰው በጉልበት ወይም በገንዘብ እንዲሁም በሀሳብ ማገዝ ይችላል:: እነዚህን ነገሮች በማቀናጀት ቀጣይነት ያለው የማይቋረጥ ድጋፍ ለማድረግ ጥረት እየተደረገ ነው:: በሌላ በኩል ክፍት በሆኑ ቦታዎች ኮንቴነሮችን በመገንባት ከኪራይ የሚገኘውን ገቢ ለድጋፍ ለማዋል ሀሳብ አለ::
ከወረዳው ጥቃቅንና አነስኛ አደራጆች ጋር በመነጋገር ኮንቴነሮች የሚገቡበትና የሚገነባበት ቦታ እንዲሰጥ እንቅስቃሴ ተጀምሯል:: ስራው ሲጀመርም አጋዥ ሰው ለመቅጠር ወይም ድጋፍ ከሚደረግላቸው ሰዎች ውስጥ አቅም ያላቸውን በ500 ወይም በ600 እንደአካባቢው ሁኔታ ቅጥር በመፈጸም ዶሮ የሚያረቡበት አንድ ቦታ ተዘጋጅቶ መቶ የሚሆኑ ዶሮዎችን ለማስገባት ዝግጅት ተደርጓል:: ድጋፍ የሚደደረግላቸውም አዕምሯቸው አርፎ ስራ እንዲሰሩ ለማድረግ እንቅስቃሴ እየተደረገ ነው::
አዲስ ዘመን የካቲት 12/2013