ፍሬህይወት አወቀ
በመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ በድምቀት ከሚከበሩ በዓላት መካከል በወርሃ ታህሳስ መባቻ ላይ የሚከበረው የክርስቶስ ልደት ወይም የገና በዓል አንዱ ነው። በዓሉ በፈረንጆቹ አዲስ ዓመት የመጀመሪያ ሳምንት የሚከበር ከመሆኑ ጋር ተያይዞ‹‹ ክሪስማስ››ን ጨምሮ ለተለያዩ መጤ ባህሎች ተጋላጭ ሲሆን ይታያል።
በመሆኑም ከበዓሉ ቀደም ብሎ ከተማዋ በተለያዩ ጌጣ ጌጦች በተንቆጠቆጡ ዛፎችና መብራቶች ሞቅ ደመቅ ትላለች። ይሁን እንጂ በዓሉን በትክክለኛው መንገድና በባህልና በትውፊቱ መሰረት የሚያከብሩ በርካታ ኢትዮጵያውያንም አይታጡም። የዘንድሮው የገና በዓል በመጤ ባህልም ሆነ በባህልና በትውፊቱ መሰረት ለሚያከብረው ለየት የሚያደርገው ነገር እንዳለ ዕሙን ነው።
የዘንድሮው የገና በዓልን ልዩ የሚያደርገው በመላው ዓለም ስጋት ሆኖ መቀጠሉን ያላባራው የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ባስከተለው ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ምስቅልቅሎሽ ውስጥ መከበሩ ነው። በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ የጠበቀ ማህበራዊ ግንኙነት ያላቸውና ኢኮኖሚያቸው ዝቅተኛ የሆኑ ሀገራት የኮሮና ቫይረስ ያሳደረባቸው ተጽዕኖ ቀላል ግምት የሚሰጠው አይደለም።
ሀገሪቱም የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ባስከተለው ጣጣ የተለያዩ ምስቅልቅሎችን አስተናግዳለች። ከዚሁ ጋር ተያይዞም ትምህርት ተቋርጦ ሰንብቷል፤ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ቤተ ዕምነትን ጨምሮ ዝግ ሆነው ከርመዋል፤ ስድስተኛው ሀገራዊ ምርጫ የሚከናወንበት ጊዜ ተላልፏል፤ በሰሜኑ የሀገሪቷ ክፍልም ተደርጎ የማይታወቅ ክህደት ተፈጽሞ ህግን የማስከበር እርምጃ ተወስዷል። ይህም ቀላል የማይባል ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ መደነቃቀፎችን ፈጥሮ ሰነባብቷል።
እንግዲህ እነዚህና መሰል ክስተቶች በተስተናገዱበት ማግስት እንዲሁም የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ስጋት ሆኖ በአዲስ መልክ በተስፋፋበት ወቅት የሚከበረው የገና በዓል ወረርሽኙን በመከላከል እንዲሆን እየተመኘን፤ ከእነዚህ ሁሉ ምስቅልቅሎሽ በኋላ ሀገሪቱ በቀጣይ ጊዜ የሚኖራት ተስፋ እንደምን ያለ ነው ስንል ላነሳነው ጥያቄ በፖለቲካ ተሳትፏቸው የጎላ ድርሻ ያላቸውን ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ማብራሪያ ሰጥተውናል። ፕሮፌሰር በየነ እንዳሉት፤ በግላቸውም ሆነ በሆነው በኢትዮጵያ ሶሻል ዲሞክራቲክ ፓርቲያቸው በሀገር ጉዳይ ተስፋ የማይቆርጡና ሀገሪቷም ብዙ ተስፋ ያላት ሀገር መሆኗን ያምናሉ።
በአሁኑ ወቅት ችግር ያለባቸውን አካባቢዎች መንግስት መፍትሔ ለመስጠት ትልቅ መስዋዕትነትን ከፍሎ ተንቀሳቅሷል። በዚህም እጅግ ከባድና ፈታኝ የነበረውን ህግ የማስከበር ሀላፊነትን በብቃት መወጣት ችሏል።
በመሆኑም ከዚህ ቀደም የህግ የበላይነትን አፍርሶ ሲያስቸግር የነበረው አካል በአሁን ወቅት ተሸንፏል። ርዝራዡም ቢሆን በሽሽት ተደብቆ ነው ያለው። በቦታውም ጊዜያዊ አስተዳደር ተቋቁሞ ክልላዊና ሀላፊነትን እየተረከበ ያለበት ሁኔታ አለ። ይህ ደግሞ የነበረውን አስቸጋሪ ሁኔታ ቀያሪና ማርሽ ለዋጭ በመሆኑ በቀጣይ የሀገሪቱን ትልቅ ተስፋ ያመላክታል።
አሁን የተጀመረው ህግን የማስከበር ዘመቻ ያለንን ነገር ይበልጥ እንድንጨብጥና ወደ ፊት እንድንጓዝ የሚያደርግ ጅምር ነው። ጅምሩ የማይቻል የሚመስለውን ሁሉ ያስቻለ እንዲሁም የአይነኬነት፣ የጠንካራነትና እኔ ያልኩት ብቻ ባይነትን በህግ የበላይነት ማስታረቅ መቻሉ ትልቅና በአጭር ጊዜ ውስጥ የተገኘ ስኬት ነው።
ይህ ስኬት ብቻ በራሱ ከተፈጠረው ውጥረትና ህገ ወጦቹ ሲያናፍሱት ከነበረው ነገር አንጻር ሲታይ በቀጣይ ሀገሪቷ ካሏት ተስፋ ሰጪ ነገሮች መካካል አንዱ ሆኗል።
ሌላው እጅግ አሳሳቢና አሳዛኝ ከሆኑ ነገሮች መካከል በቤኒሻንጉል ክልል መተከል ላይ እየሆነ ያለው ክስተት ነው። ይህንን አሳዛኝ ክስተትም መንግስት ያለ አቅሙን ተጠቅሞ ህግን ለማስከበር እየተንቀሳቀሰ ነው።
በመሆኑም የሚሰሙት ሪፖርቶች ሁሉ ከፌዴራል መንግስት አቅም በላይ የሆኑ ባለመሆናቸው ተስፋ ሰጪ የሆኑ ጅምሮች ናቸው። ይህ እየሆነ ባለበት እና በርካታ ተስፋ ሰጪ ስራዎች እየተከናወኑ ባሉበት በዚህ ወቅት ተስፋችን ላይ ጥርጣሬ የሚያጭር ምንም አይነት ነገር የለም። ምክንያቱም ኢትዮጵያ የባለ ብዙ ተስፋ ባለቤት ሀገር ናት።
ከዚህ ውጭ በሀገሪቱ የተለያዩ ችግሮች ይኖራሉ። ይሁንና ሁሉንም ችግሮች በአንድ ጊዜ ዳስሶ መጨረስ አይቻልም። ነገር ግን የችግሮቹ መጠንና ስፋት የሚለያዩ በመሆናቸው መንግስት ቅድሚያ ለሚሰጠው ቅድሚያ እየሰጠ በትኩረት እየተከታተለ እና ለችግሮች ሁሉ መፍትሔ እየሰጠ ይገኛል።
በመሆኑም በአሁን ወቅት እየታዩ ያሉትን ችግሮቹ ቀስ በቀስ መፍታት ተችሎ አይተናል። ይህም መጪው ጊዜ የተሻለ እንደሚሆን አመላካች ከሆኑት አንኳር ጉዳዮች መካከል ሆኖ ይጠቀሳል።
ከዚሁ ጋር በተያያዘም ሀገሪቷ ህዝቦቿን አግባብታ በሰላም ማኖር የምትችለው ዴሞክራሲን በማስፈን በመሆኑና የዴሞክራሲ መገለጫው ደግሞ ምርጫ ስለሆነ ለምርጫው አስፈላጊው ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል። ይህ አንዱና ተስፋ ሰጪ ከሆኑ ቁልፍ ጉዳዮች መካከል ይጠቀሳል።
በምርጫውም አብዛኛው የኢትዮጵያ ህዝብ ለተፎካካሪ ፓርቲዎች የራሱን ይሁንታ የሚሰጥበትና የሚነፍግበት ምቹ ሁኔታን መፍጠር ያስፈልጋል። ለዚህም የጀመራቸውን ሥራዎች አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ፕሮፌሰር በየነ አንስተዋል።
ይሁን እንጂ አንዳንዶች አሁን ያለው መንግስት ህዝባዊ ውክልና የሌለው ነው። ከህዝባዊ ውክልና ውጭ በሆነ መንገድ ነው ሀገሪቷን እያስተዳደረ ያለው ለማለት የሚዳዳቸው ሰዎች መኖራቸውን ያነሱት ፕሮፌሰር በየነ፤ እነዚህን እና ከእነዚህ ውጭ ያሉትን እንከኖች እንዲሁም በመካከል ያሉትን አደናቃፊዎች በጥበብ ማለፍና መፍትሔ በመስጠት ምርጫ ውስጥ መግባትና የህዝቡን ድምጽ ማድመጥ የችግሮች ሁሉ መፍትሔ እንደሚሆን ያምናሉ።
እነዚህን ማከናወን ምርጫውን ፍትሀዊ በሆነ መንገድ ማሳካት ከተቻለ ለሀገሪቱ ቀጣይ ጉዞ ትልቅ ስንቅ ከመሆኑም ባለፈ የተስፋ መገለጫም ጭምር እንደሆነ ገልጸዋል።
አንዳንዶች በሆነው ባልሆነው ጽንፍ ረግጠው መንግስትን የሚፈታተኑ አሉ። ነገር ግን ለእነዚህ አካላት የህግ የበላይነትን ማክበር እንዳለባቸው እያስተማሩ መሄድ ይገባል። ስልጣን ላይ ያለው መንግስት ህግን ከማስከበር አንጻር ይታማበት የነበረውን ክፍተት አሁን ላይ እያስተካከለ ነው።
አሁን በሀገሪቱ እየታየ ያለውን ውጥረት የሚፈጥሩት ጥቂት አመራር ነን የሚሉ ጽንፈኞች በመሆናቸው መንግስት ደግሞ እነሱን እና ሰፊውን ህዝብ ለይቷል። ጦርነቱን ማሸነፍ ብቻ ሳሆን ከጦርነቱ ባለፈ በቀጣይ የህዝቡን ችግር እየፈታና የልብ ትርታውን በማዳመጥ በመልካምነት ማሸነፍ ይቻላል። በዚህም የጊዜ ጉዳይ ይሆናል እንጂ ሁሉም ነገር ይረጋጋል።
ይሁንና የሁሉም ነገር መቋጫው ምርጫ በመሆኑ ሀገሪቱ በቀጣይ ጊዜ ለሚኖራት ተስፋ ዋናው ቁምነገር እና ፍቱን መድሃኒት ተደርጎ መወሰድ አለበት። ምርጫን ማካሄድ እና ምርጫውም መተማመን እንዲኖረውና ተአማኒ እንዲሆን በማድረግ በኩል ከፍተኛ የሆነ ጥንቃቄ ማድረግ ያስፈልጋል። ይህን ማድረግ ከተቻለ ሀገሪቱ ብዙ ተስፋ ያላት በመሆኗ መጪው ጊዜ ብሩህ ይሆናል።
ለተግባራዊነቱም መንግስት እየወሰደ ያለውን ህግን የማስከበር እርምጃ አጠናክሮ መቀጠል ይኖርበታል። በመጨረሻም ለመላው ክርስቲያን ማህበረሰብ ታላቁ የገና በዓል እንደ ታላቅነቱ የሰላም የፍቅርና የመቀራረብ ጊዜ ሆኖ እንዲያልፍ ያላቸውን መልካም ምኞት አስተላልፈዋል።
ሌላው ያነጋገርናቸው ደግሞ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትሕ ኢዜማ የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ አቶ ናትናኤል ፈለቀ ናቸው። አቶ ናትናኤል በበኩላቸው ከበዓሉ ድምቀት ባለፈ ዘንድሮ ሀገራዊ ምርጫ የሚካሄድበት ወቅት እንደመሆኑ ፖለቲካውም ሞቅ ሞቅ እንደሚል አንስተዋል። ከዚህ በፊት በሀገሪቱ በነበሩ የተለያዩ ችግሮች ምክንያት የጸጥታ መደፍረሶችና ዜጎች ላይ የሚደርስ ጉዳትና ጥቃት ነበር።
በመሆኑም በቀጣይ ሀገሪቱ በምታካሂደው ምርጫ ህዝቡ ተሳትፎ በማድረግ ለሚፈልገው ሰው ስልጣን የሚሰጥበት ይሆናል። ይህን ተከትሎም ስልጣን ላይ ያሉት ሰዎች የህዝቡን ደህንነት የማረጋገጥ እና የሀገሪቱን ሰላምና አንድነት የመጠበቅ ሥራን አጠናክረው በመሥራት ቀጣዩ ጊዜ የህዝቦች አንድነት የሚጠናከርበትና የዜጎች ደህንነት የሚረጋገጥበት እንደሚሆን ተስፋ አላቸው። ይህ ተስፋቸው ዕውን እንዲሆንም የበኩላቸውን እየተወጡ ይገኛሉ።
በቅርቡም ሀገሪቱ ካስተናገደቻቸው ያልተጠበቁ ክስተቶች መካከል በሰሜኑ ክፍል የተደረገው ህግን የማስከበር እርምጃ አንዱ መሆኑን የጠቀሱት አቶ ናትናኤል፤ አንድ እራሱን ከህግ በላይ አድርጎ የወሰደ ሀይል የነበረ ቢሆንም በህግ የበላይነት ተሸነፏል። ከዚህም በላይ የህግ የበላይነትን በማረጋገጥ ህግ የማስከበር እርምጃ መከናወኑን አንስተዋል።
ከዚህ በኋላም ሁሉም የፖለቲካ ሀይሎች በምንም አይነት ምክንያት ሀይልን በመጠቀም የፖለቲካ አመለካከታቸውን ለማራመድ የሚሞክሩበት መንገድ ሊኖር እንደማንችል እና ካለም አደጋ እንዳለውና ጠቃሚ መንገድ አለመሆኑን መረዳት ያስፈልጋል።
ከዚህ ጋር ተያይዞም የፖለቲካ ፓርቲዎች ከዚህ በኋላ የሚያደርጉት እንቅስቃሴና የፖለቲካ ትግል ሁሉ ሰላማዊና ህግን ያከበረ ይሆናል የሚል እምነት አላቻው። ያላቸው ተስፋም ከዚሁ ጋር የተያያዘና ሀገሪቱ ተመልሳ እንዲህ አይነት ችግር አዙሪት ውስጥ እንደማትገባ እምነት አላቸው። ለዚህም ምርጫው ሰላማዊና ፍትሀዊ ሆኖ የህዝቦች ሰላምና መረጋጋት የሰፈነባት የዜጎች ደህንነት የሚጠበቅባት ሀገር ትሆናለች።
መጪው ጊዜ በሀገሪቱ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ተስፋ የሚሰጥ ዜጎችን እውነተኛ የስልጣን ባለቤት የሚያደርግ ዕድል ከፊት ለፊት እንዳለ ኢዜማ ያምናል። ይሁንና ለተግባራዊነቱ መንግስትን ጨምሮ የሚመለከታቸው አካላት በሙሉ የድርሻቸውን መወጣትና ዕድሉን መጠቀም ይገባል።
ለዚህም ኢዜማ በመጀመሪያ ደረጃ የሚያደርጋቸውን ማንኛውንም እንቅስቃሴዎች በህግ ማዕቀፍ ውስጥ በማድረግ ሰላማዊ መሆናቸውን ያረጋግጣል። በሁለተኛ ደረጃ አባላቱን በምርጫ ህጉ የፖለቲካ ፓርቲዎች በጋራ በተስማሙበት የስነምግባር ሰነድ እንዲሁም እራሳቸው አዘጋጅተው ይፋ ባደረጉት የምርጫ ቁልፍ የስነምግባር መመሪያዎች በመገዛት ምርጫው ሰላማዊ ሆኖ እንዲያልፍ የበኩሉን እየተወጣ ይገኛል።
ከዚህ በተጨማሪም ከስሜታዊነት የጸዳ እና አማራጭ ሀሳቦች ላይ ያተኮረ የምርጫ ቅስቀሳ ለማድረግ ጥረት ያደርጋል። ለዚህም 43 በሚጠጉ የተለያዩ የፖሊሲ አማራጮች ላይ ባለሙያዎችን በማሳተፍ እየሰራ ነው።
ስለዚህ በቀጣይ ለሚካሄደው የምርጫ ቅስቀሳ ጥላቻን ከሚያንጸባርቁና ስሜትን ከሚነኩ ድርጊቶች የተቆጠበና አማራጭ ሀሳብ ላይ ያተኮረ እንዲሆን ይደረጋል። ይህም በቀጣይ በሀገሪቱ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ ላይ የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ተስፋ ሰጪ ጉዳዮች አንዱ እንደሆነ አመላክተው ለመላው የክርስትና እምነት ተከታይ ኢትዮጵያውያን በሙሉ መልካም የገና በዓል እንዲሆን ተመኝተዋል።
በመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ በድምቀት ከሚከበሩ በዓላት መካከል በወርሃ ታህሳስ መባቻ ላይ የሚከበረው የክርስቶስ ልደት ወይም የገና በዓል አንዱ ነው። በዓሉ በፈረንጆቹ አዲስ ዓመት የመጀመሪያ ሳምንት የሚከበር ከመሆኑ ጋር ተያይዞ‹‹ ክሪስማስ››ን ጨምሮ ለተለያዩ መጤ ባህሎች ተጋላጭ ሲሆን ይታያል።
በመሆኑም ከበዓሉ ቀደም ብሎ ከተማዋ በተለያዩ ጌጣ ጌጦች በተንቆጠቆጡ ዛፎችና መብራቶች ሞቅ ደመቅ ትላለች። ይሁን እንጂ በዓሉን በትክክለኛው መንገድና በባህልና በትውፊቱ መሰረት የሚያከብሩ በርካታ ኢትዮጵያውያንም አይታጡም። የዘንድሮው የገና በዓል በመጤ ባህልም ሆነ በባህልና በትውፊቱ መሰረት ለሚያከብረው ለየት የሚያደርገው ነገር እንዳለ ዕሙን ነው።
የዘንድሮው የገና በዓልን ልዩ የሚያደርገው በመላው ዓለም ስጋት ሆኖ መቀጠሉን ያላባራው የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ባስከተለው ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ምስቅልቅሎሽ ውስጥ መከበሩ ነው። በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ የጠበቀ ማህበራዊ ግንኙነት ያላቸውና ኢኮኖሚያቸው ዝቅተኛ የሆኑ ሀገራት የኮሮና ቫይረስ ያሳደረባቸው ተጽዕኖ ቀላል ግምት የሚሰጠው አይደለም።
ሀገሪቱም የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ባስከተለው ጣጣ የተለያዩ ምስቅልቅሎችን አስተናግዳለች። ከዚሁ ጋር ተያይዞም ትምህርት ተቋርጦ ሰንብቷል፤ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ቤተ ዕምነትን ጨምሮ ዝግ ሆነው ከርመዋል፤ ስድስተኛው ሀገራዊ ምርጫ የሚከናወንበት ጊዜ ተላልፏል፤ በሰሜኑ የሀገሪቷ ክፍልም ተደርጎ የማይታወቅ ክህደት ተፈጽሞ ህግን የማስከበር እርምጃ ተወስዷል። ይህም ቀላል የማይባል ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ መደነቃቀፎችን ፈጥሮ ሰነባብቷል።
እንግዲህ እነዚህና መሰል ክስተቶች በተስተናገዱበት ማግስት እንዲሁም የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ስጋት ሆኖ በአዲስ መልክ በተስፋፋበት ወቅት የሚከበረው የገና በዓል ወረርሽኙን በመከላከል እንዲሆን እየተመኘን፤ ከእነዚህ ሁሉ ምስቅልቅሎሽ በኋላ ሀገሪቱ በቀጣይ ጊዜ የሚኖራት ተስፋ እንደምን ያለ ነው ስንል ላነሳነው ጥያቄ በፖለቲካ ተሳትፏቸው የጎላ ድርሻ ያላቸውን ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ማብራሪያ ሰጥተውናል።
ፕሮፌሰር በየነ እንዳሉት፤ በግላቸውም ሆነ በሆነው በኢትዮጵያ ሶሻል ዲሞክራቲክ ፓርቲያቸው በሀገር ጉዳይ ተስፋ የማይቆርጡና ሀገሪቷም ብዙ ተስፋ ያላት ሀገር መሆኗን ያምናሉ።
በአሁኑ ወቅት ችግር ያለባቸውን አካባቢዎች መንግስት መፍትሔ ለመስጠት ትልቅ መስዋዕትነትን ከፍሎ ተንቀሳቅሷል። በዚህም እጅግ ከባድና ፈታኝ የነበረውን ህግ የማስከበር ሀላፊነትን በብቃት መወጣት ችሏል።
በመሆኑም ከዚህ ቀደም የህግ የበላይነትን አፍርሶ ሲያስቸግር የነበረው አካል በአሁን ወቅት ተሸንፏል። ርዝራዡም ቢሆን በሽሽት ተደብቆ ነው ያለው። በቦታውም ጊዜያዊ አስተዳደር ተቋቁሞ ክልላዊና ሀላፊነትን እየተረከበ ያለበት ሁኔታ አለ። ይህ ደግሞ የነበረውን አስቸጋሪ ሁኔታ ቀያሪና ማርሽ ለዋጭ በመሆኑ በቀጣይ የሀገሪቱን ትልቅ ተስፋ ያመላክታል።
አሁን የተጀመረው ህግን የማስከበር ዘመቻ ያለንን ነገር ይበልጥ እንድንጨብጥና ወደ ፊት እንድንጓዝ የሚያደርግ ጅምር ነው። ጅምሩ የማይቻል የሚመስለውን ሁሉ ያስቻለ እንዲሁም የአይነኬነት፣ የጠንካራነትና እኔ ያልኩት ብቻ ባይነትን በህግ የበላይነት ማስታረቅ መቻሉ ትልቅና በአጭር ጊዜ ውስጥ የተገኘ ስኬት ነው።
ይህ ስኬት ብቻ በራሱ ከተፈጠረው ውጥረትና ህገ ወጦቹ ሲያናፍሱት ከነበረው ነገር አንጻር ሲታይ በቀጣይ ሀገሪቷ ካሏት ተስፋ ሰጪ ነገሮች መካካል አንዱ ሆኗል።
ሌላው እጅግ አሳሳቢና አሳዛኝ ከሆኑ ነገሮች መካከል በቤኒሻንጉል ክልል መተከል ላይ እየሆነ ያለው ክስተት ነው። ይህንን አሳዛኝ ክስተትም መንግስት ያለ አቅሙን ተጠቅሞ ህግን ለማስከበር እየተንቀሳቀሰ ነው።
በመሆኑም የሚሰሙት ሪፖርቶች ሁሉ ከፌዴራል መንግስት አቅም በላይ የሆኑ ባለመሆናቸው ተስፋ ሰጪ የሆኑ ጅምሮች ናቸው። ይህ እየሆነ ባለበት እና በርካታ ተስፋ ሰጪ ስራዎች እየተከናወኑ ባሉበት በዚህ ወቅት ተስፋችን ላይ ጥርጣሬ የሚያጭር ምንም አይነት ነገር የለም። ምክንያቱም ኢትዮጵያ የባለ ብዙ ተስፋ ባለቤት ሀገር ናት።
ከዚህ ውጭ በሀገሪቱ የተለያዩ ችግሮች ይኖራሉ። ይሁንና ሁሉንም ችግሮች በአንድ ጊዜ ዳስሶ መጨረስ አይቻልም። ነገር ግን የችግሮቹ መጠንና ስፋት የሚለያዩ በመሆናቸው መንግስት ቅድሚያ ለሚሰጠው ቅድሚያ እየሰጠ በትኩረት እየተከታተለ እና ለችግሮች ሁሉ መፍትሔ እየሰጠ ይገኛል።
በመሆኑም በአሁን ወቅት እየታዩ ያሉትን ችግሮቹ ቀስ በቀስ መፍታት ተችሎ አይተናል። ይህም መጪው ጊዜ የተሻለ እንደሚሆን አመላካች ከሆኑት አንኳር ጉዳዮች መካከል ሆኖ ይጠቀሳል።
ከዚሁ ጋር በተያያዘም ሀገሪቷ ህዝቦቿን አግባብታ በሰላም ማኖር የምትችለው ዴሞክራሲን በማስፈን በመሆኑና የዴሞክራሲ መገለጫው ደግሞ ምርጫ ስለሆነ ለምርጫው አስፈላጊው ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል።
ይህ አንዱና ተስፋ ሰጪ ከሆኑ ቁልፍ ጉዳዮች መካከል ይጠቀሳል። በምርጫውም አብዛኛው የኢትዮጵያ ህዝብ ለተፎካካሪ ፓርቲዎች የራሱን ይሁንታ የሚሰጥበትና የሚነፍግበት ምቹ ሁኔታን መፍጠር ያስፈልጋል። ለዚህም የጀመራቸውን ሥራዎች አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ፕሮፌሰር በየነ አንስተዋል።
ይሁን እንጂ አንዳንዶች አሁን ያለው መንግስት ህዝባዊ ውክልና የሌለው ነው። ከህዝባዊ ውክልና ውጭ በሆነ መንገድ ነው ሀገሪቷን እያስተዳደረ ያለው ለማለት የሚዳዳቸው ሰዎች መኖራቸውን ያነሱት ፕሮፌሰር በየነ፤ እነዚህን እና ከእነዚህ ውጭ ያሉትን እንከኖች እንዲሁም በመካከል ያሉትን አደናቃፊዎች በጥበብ ማለፍና መፍትሔ በመስጠት ምርጫ ውስጥ መግባትና የህዝቡን ድምጽ ማድመጥ የችግሮች ሁሉ መፍትሔ እንደሚሆን ያምናሉ። እነዚህን ማከናወን ምርጫውን ፍትሀዊ በሆነ መንገድ ማሳካት ከተቻለ ለሀገሪቱ ቀጣይ ጉዞ ትልቅ ስንቅ ከመሆኑም ባለፈ የተስፋ መገለጫም ጭምር እንደሆነ ገልጸዋል።
አንዳንዶች በሆነው ባልሆነው ጽንፍ ረግጠው መንግስትን የሚፈታተኑ አሉ። ነገር ግን ለእነዚህ አካላት የህግ የበላይነትን ማክበር እንዳለባቸው እያስተማሩ መሄድ ይገባል። ስልጣን ላይ ያለው መንግስት ህግን ከማስከበር አንጻር ይታማበት የነበረውን ክፍተት አሁን ላይ እያስተካከለ ነው።
አሁን በሀገሪቱ እየታየ ያለውን ውጥረት የሚፈጥሩት ጥቂት አመራር ነን የሚሉ ጽንፈኞች በመሆናቸው መንግስት ደግሞ እነሱን እና ሰፊውን ህዝብ ለይቷል። ጦርነቱን ማሸነፍ ብቻ ሳሆን ከጦርነቱ ባለፈ በቀጣይ የህዝቡን ችግር እየፈታና የልብ ትርታውን በማዳመጥ በመልካምነት ማሸነፍ ይቻላል። በዚህም የጊዜ ጉዳይ ይሆናል እንጂ ሁሉም ነገር ይረጋጋል።
ይሁንና የሁሉም ነገር መቋጫው ምርጫ በመሆኑ ሀገሪቱ በቀጣይ ጊዜ ለሚኖራት ተስፋ ዋናው ቁምነገር እና ፍቱን መድሃኒት ተደርጎ መወሰድ አለበት። ምርጫን ማካሄድ እና ምርጫውም መተማመን እንዲኖረውና ተአማኒ እንዲሆን በማድረግ በኩል ከፍተኛ የሆነ ጥንቃቄ ማድረግ ያስፈልጋል። ይህን ማድረግ ከተቻለ ሀገሪቱ ብዙ ተስፋ ያላት በመሆኗ መጪው ጊዜ ብሩህ ይሆናል።
ለተግባራዊነቱም መንግስት እየወሰደ ያለውን ህግን የማስከበር እርምጃ አጠናክሮ መቀጠል ይኖርበታል። በመጨረሻም ለመላው ክርስቲያን ማህበረሰብ ታላቁ የገና በዓል እንደ ታላቅነቱ የሰላም የፍቅርና የመቀራረብ ጊዜ ሆኖ እንዲያልፍ ያላቸውን መልካም ምኞት አስተላልፈዋል።
ሌላው ያነጋገርናቸው ደግሞ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትሕ ኢዜማ የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ አቶ ናትናኤል ፈለቀ ናቸው። አቶ ናትናኤል በበኩላቸው ከበዓሉ ድምቀት ባለፈ ዘንድሮ ሀገራዊ ምርጫ የሚካሄድበት ወቅት እንደመሆኑ ፖለቲካውም ሞቅ ሞቅ እንደሚል አንስተዋል።
ከዚህ በፊት በሀገሪቱ በነበሩ የተለያዩ ችግሮች ምክንያት የጸጥታ መደፍረሶችና ዜጎች ላይ የሚደርስ ጉዳትና ጥቃት ነበር። በመሆኑም በቀጣይ ሀገሪቱ በምታካሂደው ምርጫ ህዝቡ ተሳትፎ በማድረግ ለሚፈልገው ሰው ስልጣን የሚሰጥበት ይሆናል። ይህን ተከትሎም ስልጣን ላይ ያሉት ሰዎች የህዝቡን ደህንነት የማረጋገጥ እና የሀገሪቱን ሰላምና አንድነት የመጠበቅ ሥራን አጠናክረው በመሥራት ቀጣዩ ጊዜ የህዝቦች አንድነት የሚጠናከርበትና የዜጎች ደህንነት የሚረጋገጥበት እንደሚሆን ተስፋ አላቸው። ይህ ተስፋቸው ዕውን እንዲሆንም የበኩላቸውን እየተወጡ ይገኛሉ።
በቅርቡም ሀገሪቱ ካስተናገደቻቸው ያልተጠበቁ ክስተቶች መካከል በሰሜኑ ክፍል የተደረገው ህግን የማስከበር እርምጃ አንዱ መሆኑን የጠቀሱት አቶ ናትናኤል፤ አንድ እራሱን ከህግ በላይ አድርጎ የወሰደ ሀይል የነበረ ቢሆንም በህግ የበላይነት ተሸነፏል። ከዚህም በላይ የህግ የበላይነትን በማረጋገጥ ህግ የማስከበር እርምጃ መከናወኑን አንስተዋል። ከዚህ በኋላም ሁሉም የፖለቲካ ሀይሎች በምንም አይነት ምክንያት ሀይልን በመጠቀም የፖለቲካ አመለካከታቸውን ለማራመድ የሚሞክሩበት መንገድ ሊኖር እንደማንችል እና ካለም አደጋ እንዳለውና ጠቃሚ መንገድ አለመሆኑን መረዳት ያስፈልጋል።
ከዚህ ጋር ተያይዞም የፖለቲካ ፓርቲዎች ከዚህ በኋላ የሚያደርጉት እንቅስቃሴና የፖለቲካ ትግል ሁሉ ሰላማዊና ህግን ያከበረ ይሆናል የሚል እምነት አላቻው። ያላቸው ተስፋም ከዚሁ ጋር የተያያዘና ሀገሪቱ ተመልሳ እንዲህ አይነት ችግር አዙሪት ውስጥ እንደማትገባ እምነት አላቸው። ለዚህም ምርጫው ሰላማዊና ፍትሀዊ ሆኖ የህዝቦች ሰላምና መረጋጋት የሰፈነባት የዜጎች ደህንነት የሚጠበቅባት ሀገር ትሆናለች።
መጪው ጊዜ በሀገሪቱ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ተስፋ የሚሰጥ ዜጎችን እውነተኛ የስልጣን ባለቤት የሚያደርግ ዕድል ከፊት ለፊት እንዳለ ኢዜማ ያምናል። ይሁንና ለተግባራዊነቱ መንግስትን ጨምሮ የሚመለከታቸው አካላት በሙሉ የድርሻቸውን መወጣትና ዕድሉን መጠቀም ይገባል። ለዚህም ኢዜማ በመጀመሪያ ደረጃ የሚያደርጋቸውን ማንኛውንም እንቅስቃሴዎች በህግ ማዕቀፍ ውስጥ በማድረግ ሰላማዊ መሆናቸውን ያረጋግጣል። በሁለተኛ ደረጃ አባላቱን በምርጫ ህጉ የፖለቲካ ፓርቲዎች በጋራ በተስማሙበት የስነምግባር ሰነድ እንዲሁም እራሳቸው አዘጋጅተው ይፋ ባደረጉት የምርጫ ቁልፍ የስነምግባር መመሪያዎች በመገዛት ምርጫው ሰላማዊ ሆኖ እንዲያልፍ የበኩሉን እየተወጣ ይገኛል።
ከዚህ በተጨማሪም ከስሜታዊነት የጸዳ እና አማራጭ ሀሳቦች ላይ ያተኮረ የምርጫ ቅስቀሳ ለማድረግ ጥረት ያደርጋል። ለዚህም 43 በሚጠጉ የተለያዩ የፖሊሲ አማራጮች ላይ ባለሙያዎችን በማሳተፍ እየሰራ ነው። ስለዚህ በቀጣይ ለሚካሄደው የምርጫ ቅስቀሳ ጥላቻን ከሚያንጸባርቁና ስሜትን ከሚነኩ ድርጊቶች የተቆጠበና አማራጭ ሀሳብ ላይ ያተኮረ እንዲሆን ይደረጋል። ይህም በቀጣይ በሀገሪቱ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ ላይ የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ተስፋ ሰጪ ጉዳዮች አንዱ እንደሆነ አመላክተው ለመላው የክርስትና እምነት ተከታይ ኢትዮጵያውያን በሙሉ መልካም የገና በዓል እንዲሆን ተመኝተዋል።
አዲስ ዘመን ታህሳስ 29/2013