
በአዲስ አበባ በንጋት ብርሃን ጉም ሲሸሽ በረራው ወደ ሰሜን ምስራቅ አቀና። ከፍ ያለው የአፍሪካ ጣሪያ ቀስ በቀስ ወደ ኋላ አፈገፈገ :: የዓለቶች ግራጫ-ቡናማ ቀለም ቀስ በቀስ ካራሚል በሚመስል ወርቃማ ቀለም ተተካ። በሰሜን ምስራቅ ኢትዮጵያ የሚገኘው የአፋር ክልል ሞቃታማ ቦታ የታላቁ የምስራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ በ45 ዲግሪ ሴንቲ ግሬድ በሚያቃጥል ሙቀት ተቀብሎናል።
የኤርታ አሌ እሳተ ጎመራ በደናኪል ሸለቆ ውስጥ ጸጥ ብሏል። እኩለ ሌሊት ላይ ወደ ተራራው ጫፍ ስንሄድ የፊት መብራቱ ጨረር በጨለማ ውስጥ ያለውን አስደማሚውን ሰርጥ ቆርጦት አለፈ። ስራመድ እግሬ ስር በግዙፉ አውሬ አከርካሪ ላይ የሚሄድ ያህል ቀዝቃዛው የላቫ ዛጎል ሲሰበር የሚሰማ ድምፅ የሚመስል ይሰማ ነበር።
ጫፍ ላይ በደረስኩ ቅጽበት የምድርን የልብ ትርታ ሰማሁ። ማግማው ይፈላና ተጠቅልሎ ወደ ጉድጓድ ይገባል። ማጋማው እየፈላ በጉድጓዱ ውስጥ እየተንከባለለ፣ እንደ ፈሳሽ ወርቅ እየፈነጠቀ፣ የፈነዳው አረፋ ትኩሱን እየረጨ ይወረውረዋል።
ይህ በቀለማት ያሸበረቀ መሬት ነው። በዳሎል፣ ጨው- አልካሊ ምድር ላይ እንደ ታዓምር ዓለም፣ መሬቱ በሚገርም ሁኔታ ቢጫማ-አረንጓዴ ነው። ወደ ፊት ስንሄድ፣ የሱሪያል መልክዓ ምድር በድንገት ወደ አይናችን ይመጣል፤ የሰልፈር አለቶች ልክ እንደ ግዙፍ እንጉዳዮች ካሉ የጨው ቅርፊቶች ይመዘዛሉ ፣ ከብርቱካናማ ቀይ ኩሬዎች ጋር በአንድ ላይ የሚፈሉ ፣ የነጭ ላባ ጫካ ፣ በጣም የሚያስደንቀው የኮባልት-ሰማያዊ ፍልውሃዎች ገንዳ፣ በደማቅ ቢጫ ሰልፈር አለቶች የተከበበ እና በእንፋሎት የሚወጣ፣ ልክ እንደንግዳ ነገር ዓይንን ይማርካል::
ፀጥ ባለ ምሽት ክፍት በሆነው በዱር ካምፕ በከዋክብት የተሞላው ሰማይ ሊደረስበት የሚችል ይመስላል። ከሚልክ ዌይ ውጪ በቢሊዮኖች ከሚቆጠሩ የብርሃን ዓመታት ርቀት ላይ የፈሰሰ ብርሃን እና ከእግሬ በታች ጥንታዊው ነባሩ የምድር ምት ይሰማኛል። በዚያን ሰዓት የተፈጥሮ አድናቆት እንደገና ይቀሰቀሳል። የጨው ክሪስታል እና የእሳተ ገሞራ ድንጋይን ነክቼ በቦርሳዬ ውስጥ ሰበሰብኩት፣ እረፍት የሌለው የአፋር የልብ ትርታ እንደገና ተሰማኝ። የሥስት ቀን ጉዞው ብዙ ነገሮች በአዕምሮዬ እንዲመላለሱብኝ አድርጓል።
በጉዞዬ ወቅት በሙቀት ውስጥ እና ብዙ ባልተሟሉ ነገሮች ባሉበት ጠንክረው ለሚሠሩት በአፍዴራ የሚገኘው የቻይና ኩባንያ ታናርሙ ኬሚካል ኢንዱስትሪያል ኃ.የተ.የግ.ማ.(ታኬኢ) ቻይናውያን ሠራተኞች ሰላምታ አቅርብሁ። ታኬኢእና ሌሎች የቻይና ኩባንያዎች በጨው ማዕድን ፕሮጀክቶች ላይ ኢንቨስት በማድረግ እንደ አፋር ባሉ ሩቅ አካባቢዎች ጠንክረው በመሥራት፣ የሥራ እድል በመፍጠር፣ የታክስ ገቢን በመጨመር እና የሀገር ውስጥ ኢኮኖሚ እድገትን አስመዝግበዋል።
የክልሉ መንግሥት ለኩባንያው ኤሌክትሪክ ለማቅረብ እና ጥልቅ ትብብርን ለማጠናከር ሁኔታዎችን እንደሚያሻሽል በመስማቴ ከልብ ተደስቻለሁ። የቻይና ሕዝብ ታታሪነት፣ ጽናት እና ጥበብ እንደ አፋር ላሉ የተፈጥሮ ባለጸጋ እና ለማደግ ካለው ፍላጎት ጋር በእጅጉ ይጣመራል ። እንዲህ ዓይነቱ ውህደት በእርግጠኝነት በዚህ ሞቃት ቦታ ላይ ተጨማሪ ተአምራት ይፈጥራል። ሁሉም የቻይና እና የኢትዮጵያ ዘርፎች ባደረጉት የጋራ ጥረት እንደ ታኬኢ ያሉ የቻይና ኩባንያዎች ባለፉት ዓመታት በመላው ኢትዮጵያ ሥር መስደድና ማበብ ችለዋል፤ ለሀገሪቱ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ዕድገት ከራሳቸው ዕድገት ጋር ትልቅ አስተዋጽኦ በማበርከት፣ የቻይናና ኢትዮጵያ የጋራ ተጠቃሚነትና አሸናፊነት ያለው ትብብር መሬት ላይ እንዲወርድ አድርገዋል።
በጉዟችን ላይ ተሽከርካሪያችንን የእሳተ ገሞራ አመድ ገንፍሎ መንገዳችንን ዘጋብን ። አብሮን የሄደው የሀገር ውስጥ ሹፌር “የአፍሪካ የመንገድ ማሳጅ” ብሎ ቀለደበት። የኋለኛው መንገድ ግንባታ በድንበር አካባቢ ያለውን አስደናቂ ገጽታ የበለጠ ከቱሪስቶች አካባቢ የራቀ ነው። ከበርካታ ሰአታት ጭላንጭል በኋላ በመጨረሻ በተስተካከለ የለሰለሰ መንገድ ላይ መሄድ ቻልን። ይህ በቻይና ኩባንያዎች እንደተሠራ ሹፌሩ ነግሮኛል።
በጨረፍታ ጠንከር ያለ እና ጠፍጣፋው የአስፓልት መንገድ ከሰማይ እይታ ጋር አብሮ የተዘረጋ ይመስላል። ለአካባቢው ነዋሪዎች እና ለቱሪስቶች ጉዞ ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል። አንድ የድሮ ቻይናዊ አባባል አለ፡ “ሀብታም ለመሆን መጀመሪያ መንገዶችን ሥሩ”። መሠረተ ልማት ለክልላዊ ልማት ወሳኝ ነው። በተሻሻለ ትብብር፣ ብዙ የቻይና ኩባንያዎች እንደ አፋር ባሉ የመሠረተ ልማት ግንባታዎች ላይ ትልቅ አስተዋፅኦ ያደርጋሉ፣ ለልማትና ብልፅግና ብዙ መንገዶችን ይገነባሉ ብዬ አምናለሁ።
የአስፓልት መንገዱ ቻይና እና ኢትዮጵያ እጅ ለእጅ ተያይዘው የሚራመዱበት የዘመናዊነት መንገድ ሆኖ ያገለግላል። ፕሬዚዳንት ሺ ጂን ፒንግ ለቻይና-አፍሪካ ማሻሻያ የሚሆኑ አስር የትብብር ሥራዎችን ሃሳብ ያቀረቡ ሲሆን ቻይና እና አፍሪካ እጅ ለእጅ ተያይዘው ወደ ዘመናዊነት መገስገስ እንዳለባቸው አሳስበዋል። ይህ ደግሞ በአፋር እና በአጠቃላይ ኢትዮጵያ ከቻይና ጋር በተሻሻለ ትብብር ልማትን ለማሳደግ ትልቅ ዕድሎችን እንደሚያመጣ ጥርጥር የለውም።
የቻይንኛ አባባል “ጉዞው እስካለ ድረስ በእርግጠኝነት በጉዞው ላይ ስንቆይ መድረሻችን እንደርሳለን” ይላል። አንድ አፍሪካዊ አባባል ደግሞ “በፍጥነት መሄድ ከፈለግክ ብቻህን ሂድ፣ ሩቅ መሄድ ከፈለግክ አብራችሁ ሂዱ” ይባላል። ባለፈው ዓመት በቤጂንግ በቻይና አፍሪካ ትብብር መድረክ የመክፈቻ ሥነ ሥርዓት ላይ ፕሬዚዳንት ሺ ጂንፒንግ ወደ ዘመናዊነት ጎዳና ማንም እና የትኛውም ሀገር ወደ ኋላ መቅረት እንደሌለበት ጠቁመዋል።
እንደማስበው፣ በኢትዮጵያ ወደ ዘመናዊነት ጎዳና፣ የትኛውም ክልላዊ መንግሥት ወደ ኋላ መቅረት የለበትም። የጥንት ሰዎች መፍለቂያ የሆነችው አፋር በአዲስ ጉልበት እያበራች ነው። በድርቅና በመካንነት መታሰር የለባትም። ቻይና ወደ ልማትና ብልፅግና ጎዳና በጋራ ለመጓዝ ከሁሉም ሴክተሮች እና ከሁሉም የኢትዮጵያ ግዛቶች ጋር ያለውን ግንኙነት ለማጠናከር ዝግጁ መሆኗን አስታውቃለች። በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ሆኜ ሥራ ከጀመርኩ ከአስር ወራት በፊት ጀምሮ በኢትዮጵያ የባሌ ተራሮችን፣ ይርጋጨፌ፣ ጅማ፣ አርባምንጭ፣ ሀረር፣ ድሬዳዋ እና ሌሎች ቦታዎችን መጎብኘቴ በጥልቅ አስደነቀኝ።
ይህ የሺህ ዓመታት ሥልጣኔ ያላት ሰፊ መሬት እና ታታሪ እና ጀግና ሕዝቦቿ ከቻይና ጋር ብዙ ተመሳሳይነት አላቸው። ቻይና፣ ኢትዮጵያ እና አፍሪካ በደቡባዊው ንቅፈ-ዓለም የዘመናዊነትን ማዕበል ለመቆስቆስና ለማምጣት ጠንክረው በጋራ ይሠራሉ። እናም ለሰው ልጅ የወደፊት የጋራ ዕድል ያለው ማህበረሰብ ለመፍጠር በምናደርገው ጥረት አዲስ ምዕራፍ ይከፍታል!
አዲስ ዘመን እሁድ ሰኔ 1 ቀን 2017 ዓ.ም