በኤርትራ የሁለት ቀናት ጉብኝት ያደረጉት የቻይናው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ዪ በኤርትራ ላይ የተጣለውን ማዕቀብ አወገዙ።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ በአንድ ፓርቲ በብቸኝነት በምትተዳደረውና በምዕራባውያን ዘንድ በተገለለችው ኤርትራ ያደረጉትን ጉብኝታቸውን ረቡዕ ከሰዓት በኋላ አጠናቀዋል። ዋንግ ከኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ጋር መወያየታቸውን እና “ስትራቴጂካዊ አጋርነታቸውን” ለማጠናከር ፕሬዚዳንቱ በቻይና ጉብኝት እንዲያደርጉ መጋበዛቸውንም የኤርትራ የማስታወቂያ ሚኒስትር የማነ ገብረ መስቀል በትዊተር ገጻቸው አስፍረዋል። የሁለቱ አገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ከስብሰባው በኋላ በጋራ በሰጡት መግለጫ “በዲሞክራሲና በሰብአዊ መብት ሰበብ በሌሎች አገራት የውስጥ ጉዳይ የሚደረግ ጣልቃገብነትን” አውግዘዋል።
“ቻይና በኤርትራ ላይ የተጣለውን ማንኛውንም ጆ ባይደን የካፒቶል ሒል ግርግር 1ኛ ዓመት ታስቦ በሚውልበት በነገው ዕለት ዶናልድ ትራምፕን በይፋ እንደሚወቅሱ ይጠበቃል። ባይደን ንግግራቸውን የሚያደርጉት በአሜሪካ የሕዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት መሰብሰቢያ አዳራሽ ነውጡ በተስተዋለበት የሕንጻው ክፍል ነው። ጆ ባይደን በንግግራቸው ለካፒቶል ሒል ግርግር ብቸኛውና አውራው ተጠያቂ ዶናልድ ትራምፕ እንደሆኑ በማያሻማ ሁኔታ ይናገራሉ ተብሏል።
ይህ እንደሚሆን የተናገሩት ደግሞ ቀደም ብለው መግለጫ የሰጡት የዋይት ሐውስ ቃል አቀባይ ጄን ሳኪ ናቸው። ባለፈው ዓመት ጥር 6 ነበር ነውጠኛ የዶናልድ ትራምፕ ደጋፊዎች በአሜሪካ ይሆናል ተብሎ በማይጠበቅ ሁኔታ ካፒቶል ሒልን ሰብረው በመግባት ብጥብጥ የፈጠሩት። ይህም በታሪክ የካፒቶል ሒል ግርግር ተብሎ እየታሰበ ነው። መርማሪዎች እስከዛሬ 725 ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ሥር አውለው ምርመራ እያደረጉባቸው ነው። ነውጠኛ የትራምፕ ደጋፊዎች ካፒቶል ሒልን ሰብረው ሲገቡ በወቅቱ የአሜሪካ እንደራሴዎች ሸንጎ ይዘው ነበር።
ይነጋገሩ የነበረውም የጆ ባይደንን መመረጥ ለማጽደቅ ነበር። ከዚህ የካፒቶል ሒል ግርግር ትንሽ ቀደም ብሎ በምርጫ ተሸንፈው የነበሩት ዶናልድ ትራምፕ ነውጠኛ ደጋፊዎቻቸውን እስከመጨረሻው እንዲፋለሙ ቀስቅሰው ነበር።
ዶናልድ ትራምፕ ያን ወቅት ምርጫው መጭበርበሩን ደጋግመው ይናገሩ የነበረበት ጊዜ ነው። ጆ ባይደን ብዙም ስለ ቀድሞው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ስም ማንሳት የሚወዱ ባይሆንም ነገ ሳተርዴይ ሆል በሚሰኘው የካፒቶል ሒል አዳራሽ በሚያደርጉት ንግግር ግን ትራምፕን በስም እያነሱ እንደሚወቅሱ ይጠበቃል። ማዕቀብ ትቃወማለች” ማለታቸውም ተገልጿል።
በኢትዮጵያ ውስጥ ካለው ጦርነት ጋር በተያያዘ የአሜሪካ መንግሥት በአራት የኤርትራ ተቋማትና በሁለት ኤርትራውያን ላይ በያዝነው ዓመት ማዕቀብ ጥሏል። ማዕቀቡ የኢትዮጵያን መረጋጋትና አንድነት እያናጋ ነው ባለው ቀውስና ግጭት ውስጥ አስተዋጽኦ አላቸው ያላቸውን የኤርትራ ተቋማትና ዜጎችን ኢላማ ያደረገ መሆኑን የአሜሪካ የፌዴራል ግምጃ ቤት በወቅቱ አመልክቷል።
በዚህም መሠረት ዕቀባው የተጣለባቸው ተቋማት የኤርትራ መከላከያ ኃይል፣ የኤርትራ ገዢ ፓርቲ ህዝባዊ ግንባር ለዴሞክራሲና ለፍትህ፣ ህድሪ ትረስ እና ሬድ ሲ ትሬዲንግ ኮርፖሬሽን ሲሆኑ ግለሰቦቹ ደግሞ አብረሃ ካሳ ነማሪያም እና ሐጎስ ገብረሕይወት ወልደኪዳን የተባሉት ናቸው። ምንጭ ቢቢሲ የታችኛው ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ናንሲ ፒሎሲ በበኩላቸው በዕለቱ ያን ነውጥ በማሰብ የሕሊና ጸሎትን ይመራሉ ተብሎ ይጠበቃል። በካፒቶል ሒል ግርግር ጥቂት ሰዎች ሞተዋል፤ 140 የሚሆኑ የጸጥታ አካላት ላይ ጉዳት ደርሷል።
ከካፒቶል ሒል ግርግር በኋላ ተሰናባች የነበሩት ዶናልድ ትራምፕ ነውጥ በመቀስቀስ በሚል ክስ ተመስርቶባቸው የነበረ ሲሆን ያን ጊዜ በሪፐብሊካኖች ተሞልቶ የነበረው ሴኔት ግን ክሱን ውድቅ አድርጎት እንደነበረ ይታወሳል። የካፒቶል ሒል ግርግር የአሜሪካ ሕዝብ በፖለቲካ ምን ያህል እየተከፋፈለ እንደመጣ ሁነኛ ማሳያ ተደርጎ በብዙ ተንታኞች ዘንድ ይወሳል። ግቢያችን ውስጥ ዝምታ የወረሳት አንድ ሴት አውቃለሁ። የቤቷ በር ገርበብ እንዳለ ነው፤ መች እንደምትተኛና መች እንደምትነቃ አላውቀውም፤ ጠዋት በሬን ስከፍት በሯን ገርበብ ብሎ አየዋለሁ፤ ማታም ወደ መኝታዬ ስሄድ በሯ እንደ ተከፈተ ነው። አንድ ልጅ አላት፤ ከነፍሷ ጋ የተላወሰ፣ እያሰበችው ወጥቶ የሚገባ። አለሟ በልጇ በኩል መሽቶ ይነጋል።
ለድንግል ማርያም እየሱስ ምን ማለት ነበር? ለሳራ የይስሀቅ ልጅነት እንዴት ይገለጻል? እድሜዋን ሙሉ ልጅ አጥታ በአመሻሽ ልጅ ያገኘት እናት ልጇን እንዴት ትገልጸዋለች? ለዚችም ሰው ልጇ ማለት እንደዛ ነው። ሰው አታይም፤ ሰውም አያያትም።
ከራሷና ከልጇ ጋር ፤ከራሷና ከዝምታዋ ጋ የምትኖር ናት። በህይወትህ ምን ተመኝተህ አጣህ ብትሉኝ የዛችን ሴት የዝምታ ትርጉም እላችኋለሁ። አንዲት ሴት፣ አንዲት እናት፣ አንዲት ምንም የሌላት ምስኪን፣ በውበትና በስርዐት ፈጣሪን በመፍራት ውስጥ የተገነባች አንዲት ነፍስ ዝም ስትል አስቡት። ዝምታዋ ውስጥ ሌላ ዝምታ አለ፤ ያንን ዝምታ ማንም ዝም ብሎት አያውቅም። ከእሷ በቀር። እሷ የሰው ልጅ ሁሉ ጥያቄ ናት፤ በእናትነቷ ውስጥ፣ በሴትነቷ ውስጥ ማንም ያልመለሰው ጥያቄ አለ። ወደ ስራ ስሄድ በበሯ አልፋለሁ፤ ከስራ ስመለስ ወደ ቤቴ የምገባውም በሯን አልፌ ነው፤ በዛ ሁሉ መመላለሴ ውስጥ አይኖቼን ወደ ቤቷ ያልሰደድኩበት ጊዜ የለም።
ግን ምንም የረባ ነገር አላየሁም። ሰው በዛ ልክ ድሀ ይሆናል? ሰው በዛ ልክ ምንም ያጣል? ራሴን እንዲህ እየጠየኩ ወጥቼ እገባለሁ። እውነት እላችኋለሁ የእሷ ቤት እንደናፈቀኝ ምንም አልናፈቀኝም። ጨዋነቷ እንደገዛኝ፣ ሴትነቷ እንደማረከኝ ምንም አልማረከኝም። እሷን ማሳቅ እግዜርን ከማሳቅ ጋር አንድ ሆኖ አግኝቼዋለሁ።
ብቻዬን ስሆን ሳላስባት የቀረሁበት ጊዜ የለም። ቤቷ ብገባ እላለሁ፣ ባወራኋት እላለሁ፣ የዝምታዋን ወዲያ እና ወዲያ በደረስኩበት እላለሁ። ከድሀ እጇ ውሀ ብጠጣ እላለሁ፣ ከድሀ መሶቧ እንጀራ ብበላ እላለሁ፣ ከድሀ ልቧ ስፍራ ባገኝ እላለሁ።
እየሱስን ሆኜ ሌማቷን በእንጀራ፣ ገንቦዋን በወይን ብሞላ እላለሁ። በመከራዋ ውስጥ ሳቅ ብሆናት እላለሁ። እውነት እላችኋለሁ እንደ እሷ ቤት ምንም ናፍቆኝ አያውቅም።
ከቤተ መንግስት ደጅ፣ ከመልካም እድል ስፍራ ሁሉ የእሷ ቤት ይናፍቀኛል። እግዜርን ባገኘው ለእኔ ያቀድከውን መልካም ነገር ሁሉ ለእሷ አድርገው እለው ነበር። ሰይጣንን ባገኘው ደግሞ ለእሷ ያሰብከውን ክፉ ነገር ሁሉ ለእኔ አድርገው እለው ነበር።
ከዛ በላይ መከራ፣ ከዛ በላይ እንግልት እንዲደርስባት አልሻምና። የሰው ልጅ ያላወቀው አንድ ጥበብ ቢኖር ድሀ ማለት የመንግስተ ሰማያት መግቢያ በር እንደሆነ ነው እላለሁ። የሰው ልጅ ያልተረዳው አንድ ማስተዋል ቢኖር የገነት ደጆች በደግነት የሚከፈቱ እንደሆነ እነግራችኋለሁ።
እግዜርን ፍለጋ የምንከራተት ብዙዎች ነን፣ ተዓምራቶቻችንን አጠገባችን ትተን ተዓምር ፍለጋ ሩቅ የምናይ ሞልተናል፤ እግዜር ድሀ ሆኖ አብሮን እንደሚኖር የምናውቅ ግን ጥቂቶች ነን። እመኑኝ ይቺ ሴት እግዜር ናት። ይቺ ሴት እግዜር ድሀ ሆኖ ናት። በየትኛውም መስፈርት ስፈሩት ይቺ ሰው የመንግስተ ሰማያት መግቢያ በር ናት። የበደላችን ስርዓት ናት። ግን አላየናትም፣ ግን አልሰማናትም። ይቺ ሴት ርህራሄ በሚሻና በተራቆተ ህይወት ውስጥ እየኖረች የእኛ ዶሮ ወጥ የሚሸታት ናት።
ሙክት ጥለን ጮማ ስንበላ፣ የላመና የሰባ ስናማርጥ እሷ ግን ርሀብተኛ ናት። ከዝምታዋ በቀር ምንም የሌላት። ይቺን ሰው ማሳቅ በምን ይለካል? የእሷ ወዳጅ መሆን በምን ይመዘናል? የእሷን ዝምታ ማድመጥ ትርጉም ምን ያህል ነው? እሷን ካወኩ ጀምሮ ራሴን አፍርሼ ሰርቻለሁ። እሷን ካወኩ ጀምሮ እኔ ነፍሴና ልቤ ሌላ ሆነናል።
እሷን ካወኩ ጀምሮ ሞልቼ መፍሰስ ጀምሬአለሁ። ብዙ ናት፤ እልፍ አእላፍ። ለካ ድህነትም የማይደረስ ስፍራ አለው። አካሏን እንጂ ልቧን ማንም ፈልጎት የሚያገኘው አይደለም። እምነቷን ማንም ፈልጎ የሚደርስበት አይደለም። ሴትነት፣ እናትነትና፣ መልካምነት መገኛቸው እሷ ጋ ነው።
ተያይተን አናውቅም፤ በአንድ ስፍራ እየኖርን ፊቷ የገሀንምን ያህል ሩቅ ነው። ምንም ነገር እንደ እሷ ፊት ርቆኝ አያውቅም። አጠገቤ ያለን ይቅርና የፈለኩትን ማንኛውንም ነገር ሳገኝ የኖርኩ ሰው ነኝ የእሷ ፊት ግን ራቀኝ፤ አጠገቤ ሆኖ፣ አፍንጫዬ ስር ተቀምጦ ፊቷ ራቀኝ። ሴትነቷ አድማስ ሆነብኝ። ሰው አታይም፤ ሰውም አያያትም።
አንድ ቀን ግን አየኋት፤ ቀይ ገላዋን የሚያሳይ ስፌቱ የተተረተረ ቀሚስ ለብሳ፣ ተረከዟ ላይ የሳሳ ሁለት አይነት ነጠላ ጫማ ተጫምታ፣ አንድ ቀን ግን አየኋት አዳፋ ያበጀ አንገት ልብስ ተከናንባ፣ ጥቁር ለግላጋ ጸጉሯን ያጋለጠ መናኛ ሻሽ አስራ፤ አንድ ጊዜ አየኋት ዝምታዋ ተፈትቶ፤ ማንም ያልሳቀውን ሳቅ እየሳቀች…።
የተፈጥሮ መልኳ ጠፋኝ፤ በሴትነቷ ውስጥ አዲስ ሰማይና ምድር አየሁ። ከግርምቴ በኋላ ‹ለካ ተፈጥሮ የእሷን ሴትነት ተደግፋ የቆመች ናት፤ እንዲህ ማለቴን አስታውሳለሁ። እንደ እሷ እናት ሆና ቆንጆ፣ ሴት ሆና መልካም፣ ድሀ ሆና ባለጸጋ አላየሁም። አንድ ቀን ደገምኳት፤ አዳፋ ነጠላዋን ተከናንባ ከቤት ስትወጣ ተከተልኳት። እንደ ባለፈው ጊዜ ንፋስና ሀሩር ገብቶ የሚወጣበት አዳፋና ጨምዳዳ ቀሚስ ለብሳለች። ነጠላ ጫማዋም አልተቀየረም። ፊቷ ከመቼውም ጊዜ በላይ ዝም ብሏል።
ነጠላዋን ትከሻዋ ላይ አጣፍታ ከአጥቢያው ገረገራ በአንዱ ጠርዝ ስትቆም አየኋት። በዝምታ እግዜርን እንዲህ የምትለው ይመስለኛል ‹ሌማቷ የተራቆተ፣ በእንስራዋ ውስጥ ዱቄት ያጣች ምስኪን ሴት ፊትህ ቆመማለች፤እባክህን ተመልከታት› የምትል።
በዚች ሴት ልባረክ አንድ ቀን በስሟ ከመስሪያ ቤቴ የሰበሰብኩትን ገንዘብ ልሰጣት ወደ ቤቷ ሄድኩ፤ እኔም እሷም እንደዛ ቀን መች ደስ እንዳለን አላውቅም። ለመጀመሪያ ጊዜ ሳቋንና ድምጽዋን ያን ቀን ሰማሁት። በህይወቴ ለመጀመሪያ ጊዜ በእሷ ደስታ እግዜርን ያስደሰትኩት ያኔ ነው እላለሁ።
በትረ ሙሴ (መልከ ኢትዮጵ)
አዲስ ዘመን ታኅሣሥ 29/2014