ወዳጄ ነገ ከቻልክ እንቅልፍ እንዳወስድህ። የሀገርህን ውብ ገፅታ፤ የህዝብህን ድንቅ ባህል ወጥተህ ታደም።ወዳጄ የቁርስ ጉዳይ አያሳስብህ የምትታደመው “እንካ ብላልኝ፤ በሞቴ ይህቺን ደህሞ ተረጎንጭልኝ” የሚል ህዝብ በደገሰው ድንቅ ባህል ነው። በባህሉ ባለሙያዎች በልዩ መልኩ የተዘጋጀ ቁርጥ ተዘጋጅቶልሀል።የኦሮሞ ጭኮ ማለት ንፁህ ቅቤ እየቆረጥክ መላፍ በለው።ይሄ ድንቅ የሆነ ማህበረሰብ “ናልኝ በሞቴ ብላ፤ ይህቺን ድገም” ብሎ ሊያጎርስህ ተዘጋጅቷል።“ቁርጡን” እየቆረጥክ በአይኖችህ አይጠገቤ የሆኑ የባህል ትርኢቶች፣ መዋደድን የሚሰብኩ ልዩ ልዩ ሁነቶችን አይተህ ትደመማለህ።አዎን ወዳጄ ነገ ሸገር ላይ የሚከበረውን ድንቅ ባህል፤ አዲስ ላይ የሚጥለቀለቀውን ማራኪ ውበት፤ ፊንፉኔ ላይ የሚታየውን ፍቅር ተቋደስ።ኢሬቻን በመታደም በብዙ ተጠቀም!
ቀጣዩን አመት በጉጉት እንድትጠብቅ የሚያደርግህ የበዛ መደመም ይገጥምሀል።አብሮህ የሚኖረውን ማህበረሰብ ድንቅ እሴት፤ የእርስ በዕርስ መዋደድና ፍቅር ትመለከታለህ።እስርህ ሆኖ ያማታውቀውን አስደናቂ ማንነት፤ አብሮህ ሆኖ ያልተላመድከውን ልዩ ክስተት ኢሬቻ ላይ ታገኘዋለህ። የሀገርህን ድንቅ ውበት፤ የህዝብህን የማይነጥፍ ድንቅ ባህል፤ የወገንህን የ አብሮነት ጥምረት ትኮመኩማለህ።
ወዳጄ ይሄን ጥሩ ገጠመኝ እንዳታልፍ፤ አብረህ ተቀላቅለህ የባህሉና የበዓሉ ባለቤት ሆነህ ፍቅርን ተላመድ።ድንቁን የሀገሬን ሰው በባህል ልብሱ አጌጦ፤ ለአምላኩ ምስጋናውን ሲያደርስ ተመልከት።ደግነቱን፣ ቀናነቱን፣ የአብሮ መኖር ጥልቅ ፍቅሩንና ህብረቱን የሚገልፅበትን ልዩ እሴቱን ታደም።በአመት አንዴ ኦሮሞ በሚያከብረውን ታላቅ የባህል መድረክ ላይ ተገኝተህ ከታላቅ ህዝብ ጋር ዋል።
አይንህ በተመለከተው ነገር ላይ ሁሉ ይደመማል።የባህል አልባሳቱን አይቶ ያደንቃል፤ የማህበረሰቡን ልዩ ልዩ ትስስራዊ መገለጫዎችን አይቶ ይደመማል።አንተ ብቻ እዚያ ቦታ ተገኝተህ ወገንህን ለማየት ያብቃህ እንጂ የምትናፍቀው ልዩ ገጠመኝ ይጠብቅሀል።“ቁርጥ” ስልህ የአገሬ ሰው ጥርስህን የሚያደክም በትግል የምታኝከው አይደለም። እየሰለቀጥህ የምታሻምደው የቅቤ ልውስ እንጂ፤ ጣዕሙ ስታስበው ምራቅ የሚያስውጥ ቁርጥ ነው።
ኢትዮጵያ ድንቅ ሀገር ናት። ህዝቦችዋም የተዋቡ፤ የዚህችን ውብ ሀገር አስደናቂ ባህሎችና ማራኪ ገፅታ አይኑን ገልጦ ላስተዋለው ልቡን ከፍቶ ላሰበ ያ’ጅባል። ከራስ አስከ እግሯ፤ ከፊት እስከ ጀርባዋ ላስተዋለ ይደመማል። ተነግሮ የማያልቅ ተዳስሶ የማይደረስ ባህልና ትውፊት ባለቤት ናት ሀገሬ፤ ኢሬቻም ከእነዚህ ሀገራዊ ድንቅ ባህላዊመገለጫዎች አንዱ ክብረ በዓል ነው።
በጋው መሬቱን በፀሀዩ ሰነጣጥቆ አፈሩን እንደ ዱቄት ሊበትነው ሲቃረብ፤ ክረምቱ ደርሶ የተራበውን መሬት በዝናብ አርሶ፤ የደረቀውን መሬት ድጋሚ ህይወት ይዘራ ዘንድ፤ ድጋሚ ምድሩ ይለመልም ዘንድ ወቅቱን ይረከባል።ክረምት የህይወት መቀጠያ፤ የመኖር ዋስትና ውሀ መፍለቂያና የዝናም ምንጭ ነውና በብርቱ ይናፈቃል። በዚህ ወቅት ኦሮሞ ልዩ ባህል አለው።የክረምቱን መምጣት ተከትሎ የሚያከብረው አምላኩን በክረትም ከሚገኝ መልካም ነገር እነዲያጎናፅፈው የሚለምንበት በክረምት ከመጣ ክፋት እንዲጠብቀው የሚማፀንበት፤ ኢሬቻ ተፈጥሮን ገርቶ፣ ምድርን አለምልሞ፣ ጤናን ጠብቆ ሀገርን አንፆ ላቆመ አምላክ ምስጋና የሚቀርብበት ድንቅ የኦሮሞ ትውፊታዊ በዓል ነው።የኢሬቻ ፍልስፍናው የሰዎችን አንድነትና መጠናከር የሚሰብክ፤ ፍቅር፤ ሰላም የሚያፀና፤ አብሮ መኖርንና መተጋገዝን የሚነግር መሆኑ ተናፋቂ በዓል ያርገዋል።ነገ ይህንን ክብረ በዓል መዲናችን ልታስተናግድ ወገብዋን አስራ ለበዐሉ ስርዐት በመትጋት ላይ ትገኛለች።በዚህ ክብረ በዓል ላይ በመገኘት አንተነትህን ከፍ አድርግ፤ በዚህ የሚሊዮኖች ስበስብ ላይ ታድመህ ባህል የፋፋቴ ያህል ሻኣ…ብሎ ሲወርድ ሁሉንም ሲያረሰርስ ተመልከት።
ባህል በራሱ የሚያንፀው የሚያቀናው ብዙ ጉዳይ አለ። ባህል የሚያወርሰው የበዛ ትርፍ መቋደስ የሚሰጠው ትልቅ ችሮታ ነው። የሌላ ’ምትለው አንድም ነገር የለም።መልካም ነገርን ሲመለከት የራስን ማድረግ መልካምነት ነው።“የአንተ ነው” ተብሎ የተሰጠህን ነገር “የእኔ አይደለም” ብሎ መግፋት ደግሞ ከባድ ጉዳይ፤ ነው፡፡ ኢሬቻ የሀገርህ ትሩፋት ከመሆን አልፎ የተባባሩት መንግስታት ደርጅት በዓለም ቅርስነት ሊመዘግበው ከጫፍ ላይ ደርሷል። አንተ የኔ አይደለም ብትል ይከብደብሀል።
የአንዱን ባህል በሌላው መከበሩ፤ የአንዱ በጎ ነገር ሌላው ዘንድ ደርሶ በጎነት ማላበሱ፤ ፍቅርን መጨመሩ እጅጉን የሚወደድ ጉዳይ ነው።እኛ ኢትዮጵያዊያን ብዙነታችንን አክብርን፤ የእርስ በእርስ ትስስራችን አጠንክርን መሄድ ወደፊት መጓዝ እንዳለብን ስያንፅ ያቆየን ባህላችን አይደል? የሚያስውበን የሚያስተሳስረን ድንቅ እሴታችን አይደል? ድንቅ ባህላችንን ከፍ አድርገን በጋራ ከፍታ ላይ እንድንደርስ መንገድ ሊሆነን የሚችል ብዙ ትሩፋት አለን።በዚያ ማትረፍን እንጂ መጉደልን እንዴት ልናስበው እንች ላለን?
ባህል በማህበረሰብ የረጅም ጊዜ ልምድ የሚዳብር የማህበረሰቡ መገለጫ ነው።ያንን ባህል ተወልዶ፤ በዚያው ተኮትኩቶ አድጎ የፈጠረውን በጎ ተፅዕኖ ለሌላው የሚተርፍ አገር አቅኚ ከሆነ ያ ባህል መልካምነቱ አይካድም።የሚሰጠው ጥቅምና የበዛ ትርፍ ባትራፊው የኔ ነው ባይነት ላይ ይወሰናል።በጎ ነገርን የጋራ ማድረግ ከጋራ የከበደ ብልጠት፤ ከመውደድ ከፍ ያለ መጋመድ ይፈጥራል።
አዎን፤ የሀገሬ ልጆች! እኛ ኢትዮጵያውያን የችግሮቻችን መፍትሄ ያለው በእኛው እጅ ላይ ነው። ተቀራርበን እንነጋገር፣ እንግባባ እንደራደር።የሚለያየን ነገር ይቀረፋል፤ ልዩነታችን የሰፋ ቢሆን እንኳን ተቀብለን አንደኛችን የሌላውን አክብረን በልዩነት ውስጥ በፍቅር እናድራለን። አንድ አመለካከት ሀገርን ቀይሮ አያውቅም።አንድነት ፍቅርና ህብረት እንጂ፤ የኢሬቻን የአንድነት ጥሪ አብሮ የመቆምን ባህል አብረን በማክበር አብረን በማስዋብ እናፅናው።ያ ነው ኢትዮጵያዊነት!
የተሟላ፤ እርስ በርስ የሚያስተሳስር ሙሉ የሆነ ውብ ባህል አለን።የጎደለው የሚሞላው ያለውን በማጉደል አይደለም። ሀገር የሚለወጠው በሰፊ ሀሳብ ነው። ሀገር ማለት የክብርህ መጎናፀፈያ፤ የችግርህ መከለያ ጥላ ናት። ለራሳችን ብለን ሀገራችንን እንውደድ! ለሀገራችን በጎ እንመኝ።የህዝቦችዋን መቀራረብ የሚያጠናክር መንገድ መፈለግ የሚያለያይ ከመፈለግ እጅጉን ይቀላል ወዳጄ።በህብረት ውስጥ የምታገኘው በጎ ተግባር ውጤቱ የጭኮ ያህል ይጥ ማል።
በአብሮነት ከቆምን፤ የእርስ በርስ ፍቅራችን ከደረጀ እመነኝ ያኔ ከፍታ ላይ እንገኛለን። ከፍታ ላይ የሚያደርሰው ደግሞ ፍቅር ብቻ ነው። አብሮነታችን በአብሮነት የታነፀ ውብ ጉዳይ ነው።“የእነሱ” የምንለው ምንም ነገር የለም። የኛ፤ የጋራችን፤ የሁላችን የምንለው የበዛ ነገር አስተሳስሮናል።የእጆችህን ጣቶች እያቸው ወዳጄ የተለያየ ቅርፅ፤ የራሳቸው ቁመትና ተግባር አላቸው። አንድ ላይ ሆነው ግን የተቃና ተግባር ይከውኑልሀል።ይሄ ትልቅ ሚስጥር ነው ወዳጄ፤ በጥልቀት ከተረዳኸው ብዙ የሚነግር፤ ባህሏን በመጠበቅ የእርስ በርስ ግንኙነታችንን በማጠናከር “ሀገሬ ክብሬ” የምንላትን ሀገር እንገንባ። ትውልድን ፍቅር በማስተማር በባህሉ የታነፀ፤ የሀገር ፍቅር የገባው፤ የህዝብ ጥቅም የሚያስቀድም ቀና እናድርግ። ለትውልዱ ሳናቋርጥ ፍቅርን መስበክ እንልመድ።በፍቅር የታነፀ ሀገሩን የሚወድ ትውልድ መግሪያው ይህ መንገድ ብቻ ነውና፤ በፍቅር ጥላ ስር ተቻችሎ ማደርና ተባብሮ ማደግ ደስታና ሀሴት ለሁሉም ይዳረሳል። በፍቅር የተጋሩት የከፋ ነገር እንኳን የለዘበ ክፉ ነው እንጂ ፅልመት የለውም።
ታደም ያልኩህ የኢሬቻ በዓል የተዋበ ባህሉን ከየአቅጣጫው አቅርቦ የሚያስኮመኩምህ ደጉ ወገኔ ውበቱንና ፍቅሩን እንድታይበት ነው።በፍቅር ደግፎ የዛሬ መገኛህ ላይ ያደረሰንህ ውብ ባህል እድትመለከት አብረህም እንደትቋደስ መፈለጌ ነው ውትወታዬ፤ የሀገርህን ውብ ባህል አውቀህ ለሌላው መተረክ ትችል ዘንድ የማህበረሰብህን ባህል፤ የወገንህ ክብረ በዓል በማስጌጥ አብረህ ዋል።
የበዛ ክብረ በዓልና ባህል የታደለች ሀገር ላይ መፈጠር በራሱ ትልቅ እድል ነው ያልኩህም በዚሁ ምክንያት ነው።የተዋበ ነገር ለመዋዋስ፤ የተጓደለን ለመሙላት በብዙ ልዩነት ውስጥ በተጋመደ አንድነት ማለፍ ትልቅ ጥቅም አለው።የራቀን ነገር እኳን አቅርቦ የኔነት ስሜት መፍጠር መልመድ በጎ ነው። ይሄ ግን የቅርብ ቅርብህ ነው። የራስህ፤ አንድነት ላይ ቆሞ ስለ አንድ ሀገር ማሰብ የላቀ ምጥቀት ነው።ቀለመ ብዙ፤ ባህለ ስብጥር መሆን መልካም ነው።
የዚህችን ሀገር ተዓምራዊነት ለመረዳት ተዓምረኛ ወይም የመጠቅህ መሆን አይጠበቅብህም ወዳጄ፤ ውበት ሞልቶ የሚፈስባት፤ የተዋበ ባህል ያለት ለመሆኑ በጓዳህ ያሉትን፤ በስርህ ያሉትን ባህልና እሴቶችዋን ተመልከት።የሀገሪቱ ውበት መገለጫ የሆኑ ልጆችዋ የየራሳቸው ልዩ ባህል ስያንፀባርቁ ተመልክተህ ብዙ ትማራለህ።
በህብረት የቆሙት ልጆቿ የየራሳቸው መልካም እሴት ተላብሰው፤ ባህልና ማንነታቸውን በተለየየ መልኩ በመግለፅና በአንድነት ቆመው የሚያስጌጧ ውብ ሀገር መሆኗን ለመስከር ባህላዊ ክብረ በዓላቸውን መታደም በቂ ነው።
እዚህች ሀገር ላይ መፈጠርህን በራሱ ትልቅ አድል ነው ያልኩህ የሚገባህ ሀገሪቱ ውስጥ ያለውን ድንቅ ነገር ስትረዳ ነው።ተዟዙረህ የምታየው በረከት የተትረፈረፈ ሆኖ ታገኘዋለህ።እርግጥ ሀገሪቱ ያላት የበዛ በረከት ልጆች ተረድተው መጠቀሙ ላይ ገና ብዙ ቢቀራቸውም፤ የበዛው ሀብትቷ ግን ሳይነኩትም ብዙ መሆኑ ያስታውቃል።የሰጡትን አጥፎ የሚመልሰው፤ የዘሩበት አለምልሞ የሚያበቅለው ለሙ መሬት ጠረኑ ይናፍቃል።
ይሄንን የምትረዳው ስትርቅ ነው ወዳጄ፡፤ የሀገር ፍቅር እና ክብር ማጣጣም የሚቻለው ከጉያዋ ሲርቁ ነው።ሀገር ጥላ ነው፤ የክፉ ቀን መሸሸጊያ፤ ባህል ደግሞ የማህበረሰብ መገለጫ፤ ባህላችንን በበጎ ተጠቅምን የጋራ መቆሚያ አውድ ማድረጉ የእኛ የምንለው ነገር እንዲበዛ ያደርግልናል።ቸር ይግጠመን!
አዲስ ዘመን መስከረም 23/2012
ተገኝ ብሩ
Pretty! This was a really wonderful post. Thanks for supplying these details.
Everything is very open with a really clear clarification of the issues. It was definitely informative. Your website is very helpful. Many thanks for sharing!
Can I simply say what a relief to discover somebody who actually understands what they are talking about on the net. You definitely realize how to bring an issue to light and make it important. More people must read this and understand this side of the story. It’s surprising you are not more popular since you most certainly have the gift.
This blog was… how do I say it? Relevant!! Finally I’ve found something which helped me. Kudos.
Good post. I learn something new and challenging on sites I stumbleupon on a daily basis. It’s always interesting to read through content from other authors and practice a little something from other websites.
I would like to thank you for the efforts you’ve put in penning this website. I’m hoping to view the same high-grade content by you later on as well. In truth, your creative writing abilities has motivated me to get my own, personal website now 😉
A motivating discussion is worth comment. I think that you should publish more about this topic, it may not be a taboo subject but generally people do not speak about these subjects. To the next! Cheers.